1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

Merga Yonas Bula
ሰኞ፣ ሚያዝያ 2 2009

የኢትዮጵያ የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ማታ የሚንቀሳቀሱ ተሽካርካሪዎች ላይ የሰዓት ገደብ ተጥሎ የነበረዉን እገዳ ቀስ በቀስ የሚያስነሳ ጥናት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን በባለስልጣኑ የህዝብ አገልግሎት ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክቴር አቶ ተስፋዬ በላቸዉ ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል። 

https://p.dw.com/p/2b05S
Äthiopien Addis Ababa Bushaltestelle
ምስል DW/Eshete Bekele Tekle

Authority Plan to Lift Ban on Night Transpot Services - MP3-Stereo

ከአዲስ አበባ በ150 ክሎሜትር ክልል ዉስጥ ያለዉ የማህበረሰቡ እንቅስቃሴ በትምህርት፣ በጤና በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች መተሳሰሩ እየጨመረ ስለ መጣ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት «በፊት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት አከባብ የነበረዉን አሁን በከፊል እስከ 2:30 እንድያገለግሉ መደረጋቸዉን» አቶ ተስፋዬ ይናገራሉ።

በአገሪቱ የህብረተሰቡ እንቅስቃሴ ኢየጨመረ ስለመጣም የማታ ትራስንፖርት አገልግሎት ቀስ በቀስ ተፈጻሚ ለማድረግ ማቀዱ አቶ ተስፋዬ ያስረዳሉ። አቶ ተስፋዬ በለስልጣኑ ከዚህ ቀደም ማታ በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ የሰዓት ገደብ ያስቀመጠበትን ዋና ዋና ምክንያቶችም አሉ ይላሉ።

ከዚህ ቀደም የአባይ ትራንስፖርት ቦርድ ሊቀመንበር ነበርኩ ያሉንና የስድስት አዉቶብስ ባለንብረት መሆናቸዉን የሚናገሩት አቶ መለሰ ክሸን የማታ ትራንስፖርትን የመፍቀድ እቅድ  ለአገሪቱ ኤኮኖሚ ጠቀሜታ አለዉ ይላሉ።

በቂ መሰረተ ልማት የለለበት፣ ማለትም የመንገድና የማብራት፣ እንዲሁም ከፍተኛ የደህንነት ችግር ያለበት አገር ዉጥ ባለስልጣኑ ማታ ላይ ተሽከርካርዎች እንዲንቀሳቀሱ ማቀዱ ተጽዕኖ እንዳለዉ የሚናገሩ አልጠፉም።

ላለፉት ጊዜያት ባለስልጣኑ በህገወጥ መንገድ ማታ ተሽከርካሪ የሚያሽከረክሩትን መቆጣጠር ቢሞክርም ጉዳዩ አስቸጋሪ ሆኖ መቀጠሉንም ዘገባዎች ይጠቁማሉ።

መርጋ ዮናስ

ኂሩት መለሰ