1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የህዳሴ ግድብ ግንባታ 3ኛ ዓመት

እሑድ፣ መጋቢት 14 2006

ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገትና የለውጥ እቅድ ለማሳካት አስፈላጊ ከሆኑት ጉዳዮች መካከል የኤሌክትሪክ አቅርቦት ትልቁን ሚና ይዞዋል። በኢትዮጵያ የኤሌክትሪኩን አገልግሎት ዘርፍ የማስፋፋቱ ስራ ከተጀመረች ብዙ ዓመታት ቢሆነውም ፣ ውጤቱ እስካሁን የሚፈለገው ደረጃ ላይ ገና አልደረሰም።

https://p.dw.com/p/1BUOA
ምስል William Lloyd-George/AFP/Getty Images

ኢትዮጵያ የሕዝቧን ፍላጎት እና ኢንዱስትሪዎችን የማስፋፋት ጥረቷን ለማርካት አሁን ያሏት ግድቦች በቂ እንዳልሆኑ በመገንዘብ በዓባይ ወንዝ ላይ 6,000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል የሚባለውን የህዳሴ ግድብ ግንባታን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጀምራለች። እአአ በ2015 ዓም በተወሰነ ደረጃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ይጀምራል የሚባለው እና እአአ በ2017 ዓም እንደሚጠናቀቅ የተነገረለት የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ አሁን ሦስተኛ ዓመት የሆነበትን ምክንያት መነሻ በማድረግ የህዳሴ ግድብ ግንባታ እና ሂደቱ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል? ተወያይተንበታል።

Blue Nile, Map, english
ምስል CC/Lourdes Cardenal

አርያም ተክሌ

ልደት አበበ