የሊቢያ ምክር ቤታዊ ምርጫ ውጤት12 ሐምሌ 2004ሐሙስ፣ ሐምሌ 12 2004በሊቢያ የቀድሞው የሽግግሩ ምክር ቤት መሪ ማህሙድ ጂብሪል የሚመሩት ለዘብተኛው የተባበሩት ኃይላት ህብረት ከሁለት ሣምንት በፊት የተካሄደው ምክር ቤታዊ ምርጫ አሸናፊ ሆነ።https://p.dw.com/p/15b9zየተባበሩት ኃይላት ህብረት መሪ ማህሙድ ጂብሪልምስል dapdማስታወቂያ በጎረቤት ቱኒዝያ እና ግብፅ እንደሆነው በሊቢያም ያሸንፍ ይሆናል ተብሎ የነበረው የሙሥሊም ወንድማማችነት ፓርቲ ያቋቋሙት የፍትህ እና የመልሶ ግንባታ ፓርቲ በምርጫው ሁለተኛነቱን ቦታ ብቻ ነው የያዘው። የተቀሩት እና አብላጫ የሆኑት 120 መንበሮች በነፃ ለሚወዳደሩ ዕጩዎች የተመደቡ በመሆናቸው፡ የትኛው ወገን አብላጫ ድምፅ እንደሚኖረው እስካሁን በግልጽ አልታወቀም። አርያም ተክሌ ነጋሽ መሀመድ