የላይቤርያ አጠቃላይ ምርጫ
ቅዳሜ፣ መስከረም 27 2004ማስታወቂያ
በካሜሩን ካለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት ወዲህ በስልጣን ላይ የሚገኙት ፕሬዚደንት ፖል ቢያ አዲሱ የሀገሪቱ ፕሬዚደንት ሆነው መመረጣቸው እንደማይቀር የፖለቲካ ታዛቢዎች ገልጸዋል። የሰባ ስምንት ዓመቱ ፕሬዚደንት ቢያ ለከፍተኛው የሀገር ስልጣን በተከታታይ አሁን በተከታታይ ለስድስተኛ ጊዜ ነው የሚወዳደሩት።
የፊታችን ማክስኞ ደግሞ እአአ ጥቅምት 11 ቀን 2011 ዓም በላይቤርያ ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ይካሄዳል። በአፍሪቃ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ ብሄር የሆኑት የላይቤሪያ ፕሬዚደንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ፕሬዚደታዊው ምርጫ ለማሸነፍ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ስልጣን በያዙበት ጊዜ የገቡትን ቃል አላሟሉም በሚል ቅር የተሰኘባቸውን ሕዝብ እምነት መልሰው ለማግኘት ብዙ ሞክረዋል። ይሳካላቸው መሆን አለመሆኑ የፊታችን ማክሰኞ ይለያል።
አርያም ተክሌ
መስፍን መኮንን