1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመንገድ አጠቃቀም ደህንነት

እሑድ፣ መጋቢት 28 2006

ለትራፊክ አደጋዎች መከሰት የመንገድ አጠቃቀም ደህንነትን ከግምት አለማስገባት ዋናዉ መንስኤ እንደሆነ ይታመናል።

https://p.dw.com/p/1BcIx
Polizisten in Dire Dawa Äthiopien
ምስል DW

ያለፈዉን ዓመት የዓለም የመንገድ ደህንነትን በሚመለከት ይፋ የሆነ ዘገባ በተሽከርካሪ የሚደርስ አደጋ ብዛት ተቀባይነት እንደሌለዉ ያመለክታል። የ182 ሃገራትን የመንገድ ደህንነት የቃኘዉ ይህ ዘገባ በየዓመቱ 1,2 ሚሊዮን ሕዝብ በዓለም ዙሪያ በአደጋ ህይወቱን እንደሚያጣ ገልጿል። ለአደጋ ከሚያጋልጡ ዋና ምክንያቶችም ጠጥቶ ማሽከርከርና ፍጥነት፤ ግንባር ቀደሞቹ ናቸዉ። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን አዉቶሞቢል በመፈብረክ ባትታወቅም የመኪና አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ከሚገኝባቸዉ ሃገራትን አንዷ መሆኗ ይነገራል። በሀገሪቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሰፋፊና ምቹ መንገዶች ከመገንባታቸዉ ጋ በተያያዘም በፍጥነት ማሽከርከር እንዲሁም የመንገድ አጠቃቀም፤ የቴክኒክ እክል ያለባቸዉ ተሽከርካሪዎች ለሥራ መሠማራት አደጋ እንዲደጋገም ምክንያት ሆነዋል። ዶቼ ቬለ በዚህ ሳምንት ለዉይይት ያቀረበዉ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የመንገድ ደህንነትና ጥንቃቄን ይመለከታል።

ሸዋዬ ለገሠ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ