የመኢአድና የአንድነት ፓርቲዎች ዉዝግብ
ሰኞ፣ መጋቢት 15 2006ማስታወቂያ
ባለፈዉ ሳምት-መጀመሪያ የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚዘግቡ መገናኛ ዘዴዎች በጣሙን ድረ-ገፆች ያሠራጩዋት ዘገባ-የኢትዮያን ፖለቲካ ለሚከታተል ባንድ ወይም በሌላ መልኩ ትኩረትን የምትስብ ነበረች።የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የኢትዮጳያ አንድነት ለዴሚክራሲና ለፍትሕ (አንድነት) የመቀራረብ ሥምምነት መጋቢት 11 ሊፈራረሙ ነዉ-የሚል ነበር-የዘገባዉ ጥቅል ጭብጥ። ሐሙስን ጠበቅን።ምንም የለም።አርብ ደወልን።ፊርማዉ የለም።እነሱም ይወዛገባሉ።
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ