1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የማሊ ቀውስ እና ኤኮዋስ

ረቡዕ፣ ኅዳር 5 2005

የምዕራብ አፍሪቃ መንግሥታት የኤኮኖሚ ማህበረሰብ፡ ኤኮዋስ ሰሜናዊ ማሊን የተቆጣጠሩትን ሙሥሊም ፅንፈኞችን ለመታገል እና የማሊን ዴሞክራቲክ ህልውና እና የግዛት ሉዓላዊነትን እንደገና ለማረጋገጥ ወደዚሁ አካባቢ 3300 ወታደሮች የተጠቃለሉበት ጠንካራ ጦር ወደ ማሊ ለመላክ ከወሰነ ጥቂት ቀናት ሆነው።

https://p.dw.com/p/16jET
General picture of an ECOWAS Summit gathering west African leaders to plot a military strategy to wrest control of northern Mali from Islamist groups as fears grow over the risks they pose to the region and beyond, on November 11, 2012 in Abuja. West African plans could see the mobilisation of some 5,500 soldiers, essentially but not totally drawn from the region. Between 200 and 400 European soldiers will train troops in Mali, according to the operational plan. AFP PHOTO / PIUS UTOMI EKPEI (Photo credit should read PIUS UTOMI EKPEI/AFP/Getty Images)
የኤኮዋስ ምክክርምስል PIUS UTOMI EKPEI/AFP/Getty Images

የተመ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት የአፍሪቃ ህብረት የሰላም እና የፀጥታ ምክር ቤት ወደማሊ የጦር ተልዕኮ የሚላክበትን ዕቅድ እአአ እስከ ህዳር ሀያ ሰባት እንዲያቀርብ ጊዜ ሰጥቶዋል። ለማሊ ውዝግብ ከጦሩ ርምጃ በፊት፡ በድርድር መፍትሔ የማስገኘቱ ጥረት እንዲቀድም የማሊን ቀውስ ለማብቃት የተነደፈው የሰላም ማፈላለጊያው ዕቅድ በግልጽ አስቀምጦዋል።

የምዕራብ አፍሪቃ መንግሥታት የኤኮኖሚ ማህበረሰብ፡ ኤኮዋስ ጦሩን ወደ ማሊ ለመላክ ዝግጅት ቢጀምርም፡ ውዝግቡ በውይይት ሰላማዊ መፍትሔ ሊገኝለት ይችላል የሚል እምነት ስላለው፡ በወቅቱ ከፅንፈኞቹ አንዱ የሆነው የአንሳር ዲን የልዑካን ቡድን የሽምግልናውን ሚና ከያዙት የኤኮዋስ ተደራዳሪ የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚደንት ብሌዝ ካምፓዎሬ ጋ እየተደራደረ ነው።
የማሊ ውዝግብ በርግጥ በድርድር መፍትሔ ማግኘት አለማግኘቱ ወደፊት የሚታይ ቢሆንም፡ እንደ ለንደኑ የቻታም ሀውስ የፖለቲካ ተቋም የአፍሪቃ ክፍል ኃላፊ አሌክስ ቫይንስ አስተያየት፡ ኤኮዋስ፡ የአፍሪቃ ህብረትም ሆኑ የተመድ ጦርነትን እንደመጨረሻ አማራጭ ነው የሚያመለከቱት።
« ይህ የሰላም ማፈላለጊያው ዕቅድ አካል ነው። ማለትም ድርድሩን በመቀጠል በማሊ የጦር ርምጃ ማስወገድ የሚቻልበትን መንገድ መፈለግ ነው። ይህ የአፍሪቃ ህብረት ባለፈው ጥቅምት ወር የደረሰው የስልታዊው መመሪያ እና የተመድ ፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ያሳለፈው ውሳኔ አንቀጽ 2071 አካል ነው። ስለዚህ የወቅቱ ዕቅድ ድርድሩን ከመቀጠሉ ጎን፡ የጦሩን ርምጃ ካስፈለገ በሚቀጥለው ዓመት መጀመር የሚቻልበትን ዝግጅት ማካሄድ ነው። »
ኤኮዋስ ግን የማሊን የግዛት ሉዓላዊነትን ከሚያከብሩ ጋ ብቻ ድርድሩን እንደሚያካሂድ በወቅቱ ቅድመ ግዴታ አስቀምጦዋል። ይህ አንዳንድ ወገኖችን የሚያገል ሊሆን እንደሚችል ነው አሌክስ ቫይን የሚገምቱት።
« በኔ አስተያየት ድርድሩ በጠቅላላ የተሳካ ውጤት ያስገኛሉ ብዬ አላስብም። ሰላማዊ መፍትሔ መድረስ የማይፈልጉ ቡድኖች ይኖራሉ። ስለዚህ በሚቀጥለው አውሮጳዊ ዓመት የጦር ርምጃ የምናይበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል። »
ኤኮዋስ በወቅቱ ይፋ ባይሆንም ብዙ የአፍሪቃ መሪዎች የተሳተፉበት የሽምግልና ጥረት መጀመሩ አዎንታዊ ነው፤ ግን በማሊ ሰላማዊ መፍትሔ የማፈላለጉ ወይም የጦሩን ርምጃ የመጀመሩ ማንኛውም ውሳኔ ከኤኮዋስ ባሻገር ሌሎች ሀገራትንም የሚመለከት በመሆኑ ጥንቃቄ እንደሚያሻው አሌክስ ቫይን ገልጸዋል።
« የማሊ ውዝግብ የኤኮዋስ አባል ያልሆኑ ሌሎች፡ በተለይ አልጀሪያ እና ሞሪታንያንንም ይመለከታል። ስለዚህ በዚሁ ረገድ የሚደረስ ማንኛውንም ስምምነት ወይም ዕቅድ በሚገባ ማስተባበር ያስፈልጋል፤ በተለይ ዕቅዱን ሞሪታንያ እና አልጀሪያ አባል ከሆኑበት ከአፍሪቃ ህብረት ጋ ማቀነባበሩ ተገቢ ይሆናል። የአፍሪቃ ህብረት የጦሩን ተልዕኮ በማስተባበሩ ረገድ ሚና መጫወቱ ባይቀርም፡ የተልዕኮውን አመራር የሚይዘው ኤኮዋስ ይሆናል። ኤኮዋስ ወደ ማሊ ስድስት ወር የሚቆይ ጦር ለመላክ ማቀዱን ባለፈው የሣምንት መጨረሻ ያስታወቀበት መግለጫም ይህንን የሚጠቁም ነው። »
ግን ኤኮዋስ ካለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ ብቻውን ሰሜናዊ ማሊን የተቆጣጠሩትን ኃይላት መደምሰስ መቻሉን የፖለቲካ ተንታኞች አጠያይቀዋል።
« ኤኮዋስ በማሊ ጉዳይ ላይ ለሚወሰደው ርምጃ ሰፋ ያለ ዓለም አቀፋዊ ድጋፍ እንደሚያገኝ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ባሳለፈው ውሳኔ ተረጋግጦለታል። ስለዚህ የሚያስፈልገው ቴክኒካዊ ርዳታ ይቀርብለታል። የማሊን ቀውስ ለማስወገድ በተነደፈው ዕቅድ የማሊን ጦር ማሠልጠን ትልቅ ሚና ይይዛል። የአውሮጳ ህብረትም በሥልጠናው ተልዕኮ፡ ፈረንሣይን የመሳሰሉ ሀገራት ደግሞ በጋራው ግንኙነት ረገድ የበኩላቸውን ሚና መጫወታቸው አይቀርም። »

ፈረንሣይ ምናልባት ወደ ማሊ ሊላክ ይችል ይሆናል የሚባለውን የኤኮዋስ ጦር በአየር ጥቃት እንደማትረዳ በትናንቱ ዕለት ግልጽ አድርጋለች። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ወደ ማሊ ለሚባለው ጦር ስምሪት የስንቅና የትጥቅ ርዳታ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገልጾዋል።

In this Thursday, Sept. 27, 2012 photo, Islamist commanders instruct 13-year-old fighter Abdullahi to man a pickup-mounted machine gun, during a meeting with an AP journalist, in Douentza, Mali. Islamists in northern Mali have recruited and paid for as many as 1,000 children from rural towns and villages devastated by poverty and hunger. The Associated Press spoke with four children and conducted several dozen interviews with residents and human rights officials. The interviews provide evidence that a new generation in what was long a moderate and stable Muslim nation is becoming radicalized, as the Islamists gather forces to fight a potential military intervention backed by the United Nations. (Foto:Baba Ahmed/AP/dapd)
ምስል AP
GettyImages 155662170 Members of a delegation of Islamist group occupying northern Mali, Ansar Dine, speak to the press on November 6, 2012 in Ouagadougou. Ansar Dine, urged Bamako and the other armed movements to engage in a political dialogue, following talks with the chief regional mediator, Burkina Faso President Blaise Compaore. AFP PHOTO / Yempabou Ahmed OUOBA (Photo credit should read Yempabou Ahmed OUOBA/AFP/Getty Images)
የቡርኪና ፋሶ ድርድርምስል AFP/Getty Images
Photo taken on August 7, 2012 shows figthers of the Islamic group Ansar Dine standing in pick-up trucks in Kidal, northern Mali. Mali's government said on August 9 that military intervention in the Islamist-held north was 'inevitable' as the jihadists defied mediation efforts. AFP PHOTO / ROMARIC OLLO HIEN (Photo credit should read Romaric Hien/AFP/GettyImages)
የአንሳር ዲን ተዋጊዎችምስል Romaric Hien/AFP/GettyImages

አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሀመድ