1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሟችዋ ኢትዮጵያዊት ህጻን ብይን በአሜሪካ

ማክሰኞ፣ ጳጉሜን 5 2005

ኢትዮጵያዊት ጉዲፈቻ ልጃቸዉን አሰቃይተዉ ገድለዋል የሚል ክስ የተመሰረተባቸዉ አሜሪካዉያን ባልና ሚስቶች በተያዘባቸዉ ወንጀል ጭብጥ የጥፋተኝነት ብይን ተወሰነባቸዉ። ለማደጎ ከኢትዮጵያ ለወሰድዋት ህጻን ሐና ዊሊያምስ በ13 ዓመትዋ ህይወትዋ እንዲያልፍ በማድረግ ጥፋተኞች ናቸዉ ሲል የወሰነዉ አንድ የአሜሪካ ፍርድ ቤት ነዉ።

https://p.dw.com/p/19fa3
Eine Statue der Justitia (auch Justizia), Göttin der Justiz, der Rechtsprechung und der Gerechtigkeit, steht auf dem Gerechtigkeitsbrunnen auf dem Römerberg in Frankfurt am Main und hält eine Waage mit zwei Wagschalen in der linken und das Richtschwert in der rechten Hand, aufgenommen am Main am 11.01.2009. Foto: Wolfram Steinberg +++(c) dpa - Report+++
የሟችዋ ኢትዮጵያዊት ህጻን ብይን በአሜሪካምስል picture-alliance/dpa

በጎ አ 2008 ዓ,ም በወላጅ ሃላፊነት በመረከብ ሃናን በጉዲፈቻ ለማሳደግ የወሰድዋት አሜሪካዉያን ቤተሰብ ልጅቱን ማሰቃየታቸዉ ማስራባቸዉ፤ እንዲሁም ከዜሮ በታች አራት ዲግሪ ሴንቲግሪድ ብርዳማ አየር ላይ እንደጣልዋት ተዘግቦአል።በሰሜናዊ ምዕራብ ፊደራል ክፍለሃገር በዋሽንግተን ግዛት ያሉ ጉዳዩን ብይኑን እንደተከታተሉ የነገሩን የህግ ባለሞያዉ ዶክተር ሼክስፒር ፈይሳ በስልክ ጠይቀናቸዉ ነበር።

አዜብ ታደሰ
ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ