1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሠማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰር

ዓርብ፣ ሚያዝያ 17 2006

ሠማያዊ ፓርቲ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ 25 ወጣት አባላቴ ታስረውብኛል፣ ፓርቲው ሥራውን በአግባቡ እንዳያካሂድም መሰናክል እየደረሰበት ነው ሲል አስታወቀ።

https://p.dw.com/p/1Bodv
ምስል DW

በአዲስ አበባ አስተዳደር የሠላማዊ ሠልፍ ማሳወቂያ ክፍል ለፊታችን እሁድ ዕለት ሠልፍ ለማድረግ አሳውቀን ሠልፉን የምናደርግበት ቦታ ቢነገረንም፤ ፖሊስ ግን በሥራችን ላይ እንቅፋት እየፈጠረ ነው ሲል ፓርቲው ወቅሷል። ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር ስለሁኔታዉ የፓርቲዉን ሊቀመንበር አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል። ይህ ዘገባ ከተጠናቀረ በኋላ የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተዉ ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዚደንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት፤ ምክትል ፕሬዚደንቱ አቶ ስለሺ ፈይሳ እንዲሁም የፓርቲዉ የሕዝብ ግንኙነት አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ለቅስቀሳ ከፓርቲዉ ጽህፈት ቤት ሲወጡ በፖሊስ ተይዘዉ ተወስደዋል።

ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ