1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሩስያ ርዳታ እና የዩክሬይን ቅድመ ግዴታ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 6 2006

ዩክሬይን በሀገርዋ ምሥራቃዊ ከፊል በመንግሥቱ ጦር እና በዓማፅያን መካከል በቀጠለው ውጊያ ሰበብ የመሠረታዊ አቅርቦት ችግር ላጋጠመው ያካባቢው ነዋሪ ሩስያ በ280 የጭነት ተሽከርካሪዎች አጀብ ሰብዓዊ ርዳታ ልካለች፣

https://p.dw.com/p/1Ct7Z
Konvoi russischer Lastkraftwagen mit Hilfsgütern
ምስል AFP/Getty Images

ይሁንና፣ ይኸው ርዳታ ለተቸገረው ሕዝብ የሚከፋፈልበትን አሰራር በተመለከተ ዩክሬይን የራሷን ቅድመ ግዴታ አስቀምጣለች። በቅድመ ግዴታው መሠረት፣ ርዳታው እንዲገባ የሚፈቀደው ርዳታው በድንበሩ ላይ ሲራገፍ እና በዓለም አቀፍ የቀይ መሥቀል ማኅበር ትብብር እንዲከፋፈል ሲደረግ ብቻ መሆኑን የዩክሬይን መንግሥት አስታውቋል። የሩስያ የጭነት ተሽከርካሪዎቹ አጀብ የሰብዓዊ ርዳታ ነው በሚል ላማፅያኑ ርዳታ ይዞ ሊገባ ይችላል በሚል ስጋት ነው ዩክሬይን ይህን ቅድመ ግዴታ ያቀረበችው።

ዣኔት ዛይፈርት

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ