1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሮሽቶኩ ጥቃት 20ኛ አመት መታሰቢያ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 17 2004

በጀርመንዋ የወደብ ከተማ ሮሽቶክ የዛሬ 20 አመት በስደተኞች ላይ የተፈፀመው ዘረኛ ጥቃት በትናንትናው እለት በመላ ጀርመን ታስቧል ። በወቅቱ ሆ ብለው የተነሱ ወጣት አመፀኞችና ቀኝ አክራሪዎች፣ የተገን ጠያቂዎች የመኖሪያ ህንፃን በእሳት በማቃጠል ያደረሱት ጥቃት

https://p.dw.com/p/15veb
Ein Mann steht am 27.08.1992 vor brennenden Pkw auf einer Straße am zentralen Asylbewerberheim von Mecklenburg-Vorpommern in Rostock-Lichtenhagen. Vom 22. bis 28. August 1992 randalierten bis zu 1.200 meist jugendliche rechtsradikale Gewalttäter vor dem Zentralen Asylbewerberheim Mecklenburg-Vorpommern in Rostock-Lichtenhagen. Unter dem Beifall von bis zu 3000 Schaulustigen und vielen Fernsehkameras bewarfen die Rowdies das überwiegend mit Rumänen belegte Hochhaus (Sonnenblumenhaus) sowie die Polizisten mit Steinen und Brandsätzen. Foto: Bernd Wüstneck
ምስል picture-alliance/dpa

በጀርመንዋ የወደብ ከተማ ሮሽቶክ የዛሬ 20 አመት በስደተኞች ላይ የተፈፀመው ዘረኛ ጥቃት በትናንትናው እለት በመላ ጀርመን ታስቧል ። በወቅቱ ሆ ብለው የተነሱ ወጣት አመፀኞችና ቀኝ አክራሪዎች፣ የተገን ጠያቂዎች የመኖሪያ ህንፃን በእሳት በማቃጠል ያደረሱት ጥቃት ከ2ተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ ጀርመን ውስጥ ከተፈፀሙት መሰል ጥቃቶች የከፋው ነበር ። ይህ እርምጃም በጀርመን ከባድ መዘዞችን አስከትሏል ።

ሮሽቶክ በተባለው በሰሜን ምሥራቅ ጀርመንዋ የወደብ ከተማ የሚገኝ የስደተኞች መኖሪያ ህንፃ ላይ ቀኝ ፅንፈኞችና የአካባቢ ነዋሪዎች ዘግናኝ ጥቃት የፈፀሙት እጎአ ነሐሴ 22 1992 ነበር ። ጥቃቱ የደረሰበት ህንፃ  በሰሜን ጀርመኑ የሜክለንቡርግ ቮርፖመርን ፌደራዊ ክፍለ ሃገር በስደተኞች መቀበያ ማዕከልነት የሚያገለግል ስፍራ ነበር ። በወቅቱ ቀኝ ፅንፈኞች መፈክሮችን እያሰሙ ከህንፃው ሰው እንዳይወጣና እንዳይገባ በመከልከል ድንጋይ ና በነዳጅ የተሞሉ በእሳት የተያያዙ ጠርሙሶችን ወደ ህንፃው በመወርወር ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ። ወጣቶቹ ህንፃውን ሲያቃጥሉም በአካባቢው ይተላለፉ የነበሩ ሰዎች አድናቆታቸውን ይገልፁላቸው ነበር ። በሮሽቶክ የውጭ ዜጎች ጉዳይ ሃላፊ ቮልፍጋንግ ሪሽተር ጥቃቱ በተባባሰበት ወቅት ህንፃው ውስጥ ነበሩ ። 

In der Nacht zum 27. August 1992 schirmt die Polizei das inzwischen geräumte und teilweise abgebrannte Asylbewerberheim in Rostock-Lichtenhagen ab und nahm Randalierer fest. Vom 22. bis 28. August 1992 randalierten bis zu 1.200 meist jugendliche rechtsradikale Gewalttäter vor dem Zentralen Asylbewerberheim Mecklenburg-Vorpommern in Rostock-Lichtenhagen. Unter dem Beifall von bis zu 3000 Schaulustigen und vielen Fernsehkameras bewarfen die Rowdies das überwiegend mit Rumänen belegte Hochhaus sowie die Polizisten mit Steinen und Brandsätzen. Foto: Jens Kalaene
ምስል picture-alliance/dpa

« የመኖሪያውን ህንፃ ከውጭ ሆነን ስንመለከተው በዛ ያሉ በሺህ የሚቆጠሩ ያገኙትን ያለ ምህረት በማጥፋት ስሜት ተነሳስተው ነበር የሚያጠቁት ። እኛም በወቅቱ ጥቃት ደርሶብናል ምንም አዙሮ ማየት ማመዘን የሌለበት ጥቃት ነበር የተሰነዘረው ። መቶ ሰው በዚያ ቤት ውስጥ ኖረ አልኖረ ጉዳያቸው አልነበረም ። እኛም በዚያ ውስጥ ልንገደል እንችል ነበር ። » 

በሚያስገርም ሁኔታ በእሳት ቃጠሎ የተጎዳ ሰው አልነበረም ። ነዋሪዎቹ ወደ ህንፃው ጣሪያ በመሸሽ ከእሳቱ ማምለጥ ችለዋል ። ጥቃቱ ቀጥሎ ከ 2 ቀንና ለሊት በኋላ ነበር የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ስደተኞቹን ወደ ሌላ ስፍራ ለማጓጓዝ የበቁት ። ከዚያ በኋላም ቢሆን አመፀኞቹ ህንፃው ውስጥ በቀሩት ቬይትናማውያንና በፖሊስ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን አላቆሙም ። ዘግይቶ በስፍራው የደረሰው ፖሊስ አመፀኞችን በመያዝ ሁኔታውን ለመቆጣጠር ቢሞክርም ከአቅሙ በላይ ነበር የሆነው ። ከሁለቱ ጀመኖች ውህደት በኋላ ሥራ አጥነት በተስፋፋበት በምሥራቅ ጀርመን ሆድ ለባሰው ህዝብ ፖለቲከኞች ሁኔታዎችን ከማርገብ ይልቅ ስደተኞች በብዛት ወደ ጀርመን ገቡ በማለት የተጋነኑ መልእክቶችን ማስተላለፋቸው ወጣቶቹ ጥቃቱን እንዲፈጽሙ በማነሳሳት የበኩሉን አስተዋጽኦ አድርጓል ይላሉ ሪሽተር ። 

Archivfoto / Greifswald (Mecklenburg-Vorpommern): Wachablösung in einem Fenster der Unterkunft für Asylbewerber in Greifswald-Ladebow. Unbekannte Asylbewerber übergeben sich ein Messer zum Schutz vor randalierenden Jugendlichen, die das Heim am 28.08.1992 angegriffen hatten. Die Polizei hat die Lage um das Gebäude, das auch evakuierte Ausländer aus Rostock-Lichtenhagen beherbergt, jedoch unter Kontrolle. In Rostock-Lichtenhagen war es seit dem 22.08.1992 fünf Nächte lang zu ausländerfeindlichen Ausschreitungen rechtsradikaler Jugendlicher gekommen. (MvpLD6-300892)
ምስል picture-alliance/dpa

« ራድዮውም ቴሌቪዥን መመልከት በቂ ነበር ። ስደተኞች ይጎርፋሉ መርከቡ ጢም ብሎ, ሞልቷል እየተባለ ና ተገን ጠያቂዎችም ወንጀለኛ መሆናቸው ይነገር ነበር ። ይህም ለእነርሱ የጥቃት እርምጃ አስተዋጽኦ አድርጓል ። በግልፅ የሚስተዋል ነበር የቀኝ ኃይሎች ከ 2ተኛው ቀን አንስቶ ጉዳዩን የመነጋገሪያ ርዕስ ከማድረጋቸውም በላይ ጥቃት ወደ ሚፈፀምበት  ሮሽቶክ እንደ ቱሪስት ይሄዱ ነበር ። ለዚህ እርምጃም ዘረኝነትና የውጭ ዜጎች ጥላቻ እንደገፋፋቸው በሚያቀርቡት የመከራከሪያ ሃሳብ ሁሉ ይናገሩ ነበር »

ጥቃቱ ተባብሶ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሊደርስ የቻለበት ምክንያት አሁንም ያጠያይቃል ። በበርሊኑ ነፃ ዩኒቨርስቲ ዘረኝነትን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ጥናት የሚያካሂዱት ሃዮ ፉንከ አመጹ ርስ በርስ የተያያዙ ድክመቶች ውጤት ነው ይላሉ ።

« እንደ እኔ ትዝብት ወሳኙ ጉዳይ የከተማዋ አስተዳደር የፊደራል ክፍለ ሃገር እንዲሁም በከፊልም ቢሆን የፌደራሉ መንግሥት በሊሽተንሃገን ጥቃቱ እንዲባባስ አድርገዋል ። ማድረግ የሚገባቸውን በቂ እርምጃ አልወሰዱም። ስለዚህ ጥቃቱን ለ ለማስቆም የፖለቲካ ፈቃደኝነት ባለመታየቲ ስህተት ተሰርቷል ስለዚህ ባለሥልናቱ እያወቁ አንዲህ አይነት የማጥፋት ሙከራ ሲደረግ ተመልክተዋል »  

Schaulustige an der Güstrower Straße in Rostock-Lichtenhagen vor dem Zentralen Asylbewerberheim von mecklneburg-Vorpommern in dem aus DDR-Zeiten stammenden Neubaugebiet. Vom 22. bis 28. August 1992 randalierten hier bis zu 1200 meist jugendliche rechtsradikale Gewalttäter. Unter dem Beifall von bis zu 3000 Schaulustigen und vielen Fernsehkameras bewarfen die Rowdies das überwiegend mit Rumänen belegte Hochhaus sowie die Polizisten mit Steinen und Brandsätzen. Foto: Bernd Wüstneck
ምስል picture-alliance/dpa

ለአመጹ ፖለቲካዊ ምላሽ የተሰጠው ዘግይቶ ነው ። በአመፁ ተጠያቂ የተባሉ 44 ሰዎች ከ 1 እስከ 3 አመት የሚደርስ እስራት ተበይኖባቸውል ። የዚያን ጊዜው የሮሽቶክ ከንቲባና የሜክለንቡርግ ቮርፖመርን ፊደራዊ ክፍለ ሃገር የሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ከሥልጣናቸው ለመውረድ ተገደዋል ። እስካሁን ግን በተመሰቃቀለው የፖሊስ የወቅቱ ዘመቻ ተጠያቂው የማን እንደሆነ ግልፅ አይደለም ። የመኖሪያ ህንፃ ውን ከጥቃት እንዲከላከል የተሠማራው የፖሊስ ኃይል ከስፍራው ሲለቅ በምትኩ ሌላ ሳይተካ ከቀረ በኋላ ነበር አመጹ ተባብሶ ብዙ ጉዳት የደረሰው ።   

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ