1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰማያዊ አመራር አባላት የፍርድ ቤት ችሎት

ረቡዕ፣ መስከረም 5 2008

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ የወንጀል ምድብ ችሎት በብርሃኑ ተክለ ያሬድ መዝገብ በተከሰሱ አራት የሰማያዊ አመራር አባላት ላይ ብይን ለመስጠት ዛሬ ቢሰየምም ለውሳኔው ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ።

https://p.dw.com/p/1GXSy
Gericht Gesetz Jura Hammer Waage
ምስል fotolia/junial enterprises

[No title]

ፍርድ ቤቱ ድንበር አቋርጠው ወደ ግንቦት ሰባት ሊቀላቀሉ ሲሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው የተገለፀው እነዚሁ ተከሳሾች ዛሬ ያቀረቡትን አቤቱታም አዳምጧል ። ተከሳሾቹ እነ ብርሃኑ በማረሚያ ቤት እርስ በእርሳችን እንዳንገናኝ እና ህክምና እንዳናገኝ ተከልክለናል ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል ።ጉዳዩን ያዳመጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ የወንጀል ምድብ ችሎት ፤ይህ አስተዳደራዊ ችግር እንደሆነ በመጥቀስ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች እንዲያስተካክሉ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ዩሀንስ ገብረ እግዚአብሔር

ልደት አበበ

ሂሩት መለሰ