የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት በዋስ መለቀቅ9 ኅዳር 2006ሰኞ፣ ኅዳር 9 2006በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ እንዲቆም የሚጠይቅ ሰልፍ አደራጅታችኋል የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ ሌሎች የአመራር አባላት እና ደጋፊዎች በዋስ መለቀቃቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያስረዳል።https://p.dw.com/p/1AKN4ምስል DWማስታወቂያ የአመራር አባላቱ ያልተፈቀደ ሰልፍ በማደራጀት ሁከት እና ብጥብጥ ፈፅማችኋል ፣ ፀረ አረባዊነት ዓላማ ያለው ሰልፍ አደራጅታችኋል የሚል ወቀሳ ቀርቦባቸው የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ መታወቂያ እያሳዩ በዋስ መፈታታቸውን የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂኒየር ይልቃል ጌትነት ለዶይቼ ቬለ ገልፀዋል። ለዝርዝሩ ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር። ልደት አበበ ዮሐንስ ገብረግዚአብሄር አርያም ተክሌ