1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰማያዊ ፓርቲ የሕግ አገልግሎት ኃላፊ ታሰሩ

ማክሰኞ፣ መስከረም 10 2009

የሰማያዊ ፓርቲ የሕግ አገልግሎት ኃላፊ አቶ አዲሱ ጌታነህ መታሰራቸዉ ተነገረ። የፓርቲዉ ሊቀመንበር ኢንጂኔር ይልቃል ጌትነት አዳዲስ ከሚባሉት ወጣት አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ አዲሱ ትናንት ፍርድ ቤት ቀርበው ሲወጡ ማየታቸውን፤

https://p.dw.com/p/1K5Vf
Blick aus meinem Fenster Addis Abeba Äthiopien
ምስል Solomon Mengist


እና ማዕከላዊ ምርመራ እንደተያዙ ማረጋገጣቸውን ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል። የአቶ አዲሱ ቤተሰቦች በበኩላቸዉ፤ አቶ አዲሱ በባሕርዳር የፓርቲዉ አስተባባሪ ሆነዉ በማገልገል ላይ ሳሉ በተደጋጋሚ ይታሰሩ እንደነበር ገልፀዋል። አቶ አዲሱ ጌታነህ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ምርመራ መታሰራቸዉ ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቻቸዉ በጭንቀት ላይ መሆናቸዉን አዲስ አበባ የሚገኘዉ ወኪላችን ዘግቧል።


ዮሐንስ ገብረግዚአብሔር


አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ