1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሱዳን አጠቃላይ ምርጫ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 4 2002

16 ሚሊዮን ሱዳናዉያን ይሳተፋሉ በሚል የተገመተዉ የሱዳኑ አጠቃላይ ምርጫ ትናንት ተጀምሮአል። ሱዳናዉያን ከማለዳ ጀምሮ በከፍተኛ የመምረጥ ፍላጎት ወደ ምርጫ ጣብያ ሲሄዱም መስተዋሉ ተጠቅሶአል።

https://p.dw.com/p/MuUo
ምስል AP

የምርጫ ጣብያዎች ተጨናንቀዉ መታየታቸዉ እንዲሁም በምርጫ ዙርያ መጠነኛ ችግሮች መታየታቸዉ ሲነገር ይኸዉም የምርጫ ሳጥን በሰአቱ አለመድረስ እና መዘበራረቅ የተመራጮች ስም በትክክል ወረቀት ላይ አለመስፍር ከታዪት ችግሮች ገሚሶቹ መሆናቸዉ ተጠቅሶአል። ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ከሳዉዲ ዘገባ ልኮልናል

ነብዩ ሲራክ ፣ አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ