1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሴራልዮናዊው ተገን ጠያቂ አሟሟትና አወዛጋቢው ብይን

ሐሙስ፣ ጥር 7 2001

ሴራልዮናዊው ኡሪ ጃሎህ በተያዘበት ክፍል ውስጥ ከነበረ ፍራሽ በተነሳ ዕሳት ሰበብ በተያዘበት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ጥር ሰባት ሁለት ሺህ አምስት ዓመተ ምህረት በታሰረበት ክፍል እጅና እግሩ እንደተጠፈረ ሊኖርባት የጓጓላትን ምድር እስከወዲያኛው ተሰናበተ ።

https://p.dw.com/p/GZP5
ምስል AP

ከጀርመንና ከጀርመን ውጭም የበርካታ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችን ትኩረት ስቦ የቆየው ይኽው ጉዳይ ከሃያ ሁለት ወራት የፍርድ ሂደት በኃላ ባለፈው ወር በፌደራዊ ክፍለ ሀገሩ ፍርድ ቤት ብይን ተሰጥቶበታል ። ፍርድ ቤቱ በዚሁ ብይን በሰውነት ላይ ለሞት የሚያበቃ ጉዳት በማድረስ እንዲሁም ህይወት በማጥፋት ክስ ከቀረበባቸው ፖሊሶች በአንዱ ላይ የገንዘብ ቅጥት ሲወስን ሌላኛውን ደግሞ ጥፋተኛ አይደለም ሲል በነፃ አሰናብቷል ።