1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የስደተኞቹ እልቂት እና የአውሮጳ አስተያየት

ሰኞ፣ ሚያዝያ 12 2007

በሜድትሬንየን ባህር ከሊቢያ የባህር ዳርቻ ወደ ኢጣልያ በመጓዝ ላይ የነበረች መርከብ ከትናንት ወዲያ ባጋጠማት የመስመጥ አደጋ 950 ያህል ስደተኞች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተነገረ።

https://p.dw.com/p/1FBIq
Luxbemburg EU Außenminister Krisentreffen Flüchtlinge Mittelmeer
ምስል picture-alliance/dpa/J. Warnand

ከኢጣልያዊቷ የላምፔዱዛ ደሴት 110 ኪሎ ሜትር ሲቀራት ከሰመጠችው መርከብ እስካሁን 28 ሰዎችን ብቻ ማዳን መቻሉን እና 24 አስከሬኖች ማውጣታቸውን የባሕር ጠረፍ ጠባቂዎች አስታውቀዋል። የአውሮጳ ህብረት አባል ሀገራት ይህ ሁሉ ሰው በደጃፋቸው እየሞተ ርምጃ እንዲወስዱ ጫና አርፎባቸዋል።

Griechenland - Füchtlinge vor Rhodos
ምስል REUTERS/Argiris Mantikos/Eurokinissi

ካለፈው ጥር ወር ወዲህ እንኳን ወደ ሁለት ሺህ የሚጠጉ ስደተኞች ናቸው ህይወታቸው ያለፈው። እልቂቱን ምክንያት በማድረግ በወቅቱ የአውሮጳ ህብረት የውጭ ጉዳይ እና ሀገር አስተዳደር ሚንስትሮች በሉግዘምቡርግ ስብሰባ ይዘዋል። አውሮጳውያኑ ስለስደተኞቹ እልቂት ምን እያሉ ነው? ቀደም ሲል የብራስልሱን ወኪላችን ገበያው ንጉሤን በስልክ ጠይቄው ነበር።

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ