1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የስደተኞች ጥያቄ እና የአውሮጳ ጭንቀት

ረቡዕ፣ ጥር 11 2008

እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከሆነ በዓለም ዙሪያ 60 ሚሊዮን ስደተኞች ይገኛሉ። ወደ አውሮጳ ከተሰደዱት መካከል ጀርመን በርካታቶችን ወደ ሀገሯ በማስገባት ቀዳሚነቱን ስፍራ ይዛለች።

https://p.dw.com/p/1HhL2
Europaparlament Jean-Claude Juncker Debatte
ምስል Reuters/V. Kessler

ይሁንና በስደተኞች ጥያቄ ውዝግብ ላይ ያለችው ሀገር ፖለቲከኞች በአሁኑ ሰዓት ድንበር ይዘጋ አይዘጋ ክርክር ላይ ናቸው። ይሄው የስደተኞች ጉዳይ ዳቮስ -ሲውዘርላንድ ውስጥ በመካሄድ ላይ የሚገኘው የዓለም የምጣኔ ኃብት መድረክ ዋና የመወያያ ርዕስ ነው። የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ዩሀይም ጋውክ ዛሬ በተለይ የምስራቅ አውሮጳ ሀገሮች የስደተኞችን የተገን ጥያቄ በተመለከተ ትብብር እንዲያሳዩ ጠይቀዋል። አሳሳቢው የስደተኞች ጉዳይን አስመልክቶ፤ በጀርመን እና በአጠቃላይ በአውሮጳ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ወኪሎቻችንን፤ ከበርሊን ይልማ ኃይለሚካኤልን እና ከብራስልስ ገበያው ንጉሴን አነጋግረናል።

ይልማ ኃይለሚካኤል/ ገበያው ንጉሴ

ልደት አበበ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ