1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማልያ መንግስት ጥቃት እና አል ሸባብ

ማክሰኞ፣ የካቲት 29 2003

የሶማልያ ሽግግር መንግስት እና መፍቀሬ የሽግግሩ መንግስት ኃይላት በአል ሸባብ ሰፈሮች አንጻር ጠንካራ የጥቃት ዘመቻ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።

https://p.dw.com/p/R7Jg
ምስል AP

ባለፈው ሳምንት በተጀመረው ጥቃት መደዳ በመዲናይቱ ሞቃዲሾ በተካሄደው ብርቱ ውጊያ በአል ሸባብ ቁጥጥር የነበረ ሰፊ አካባቢ መያዛቸውን እየገለጹ ነው። በጥቃቱ መጠናከር የተነሳም ከአል ሸባብ ጎን ሆነው ሲዋጉ ነበር የተባሉ የውጭ ዜጎች የሆኑ ታጋዮች ከሶማልያ እየሸሹ መሆናቸው ተመልክቶዋል።

ዘሪሁን ተስፋየ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ