1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአሸባሪነት የተከሰሱ ተፈረደባቸው

ዓርብ፣ ሰኔ 16 2009

የቀድሞ የመኢአድ እና የአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ ከ4 ዓመት ከ2 ወር እስከ 4 ዓመት ከስድስት ወር እሥራት ተበየነባቸው።

https://p.dw.com/p/2fHQE
Äthiopien Journalisten Martin Schibbye und Johan Persson
ምስል AP

Beri AA (Gerichtsurteil) - MP3-Stereo

የኢትዮጵያ ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት አቃቤ ህግ በአሸባሪነት በከሰሳቸው በቀድሞ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ እና የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ አባላት ላይ ዛሬ ከ4 ዓመት ከ2 ወር እስከ 4 ዓመት ከስድስት ወር እሥራት በየነ። ችሎቱ የአረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀመንበር አብርሐ ደስታ እና የቀድሞው የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ(አንድነት) ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል ዳንኤል ሺበሺን ጉዳይ ለመመልከት ተሰይሞ ነበር። ሆኖም ዳንኤል ሺበሺ የመከላከያ ምስክሮች ሲያቀርቡ አብርሃ ደስታ ግን ችሎቱ ላይ አልተገኙም።  ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ