1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቆጵሮስ የገንዘብ ቀውስና መዘዙ

ረቡዕ፣ መጋቢት 11 2005

የአውሮፓ ህብረት ለቆጵሮስ በሚሰጠው ብድር ላይ የሚነጋገረው ኒቆስያ አማራጭ የመፍትሄ እቅዶችን ካቀረበች ብቻ መሆኑን አስታወ4ል ። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የህብረቱ ባለሥልጣን ኒቆስያ ተጨባጭ አማራጮችን እስካላቀረበችለት ድረስ ህብረቱ በጉዳዩ ላይ ዳግም እንደማይመክር ተናግረዋል ።

https://p.dw.com/p/180nZ
2010-11-03 ZOETERMEER - **ILLUSTRATION** The National flag of Cyprus, in the capital Nicosia. ANP XTRA LEX VAN LIESHOUT
ምስል picture-alliance/ANP XTRA

የአውሮፓ ህብረት ለቆጵሮስ ያወጣውን የብድርና የገንዘብ እርዳታ ስምምነት የሃገሪቱ ፓርላማ ውድቅ ካደረገው በኋላ ፣ ህብረቱ በጉዳዩ ላይ የሚነጋገረው ኒቆስያ አማራጭ የመፍትሄ እቅዶችን ካቀረበች ብቻ መሆኑን አስታወቀ ። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የህብረቱ ባለሥልጣን ኒቆስያ ተጨባጭ አማራጮችን እስካላቀረበችለት ድረስ ህብረቱ በጉዳዩ ላይ ዳግም እንደማይመክር ተናግረዋል ። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ የአውሮፓ ህብረት ፣ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክና የዓለም የገንዘብ ድርጅት ለቆጵሮስ ከቅድመ ግዴታ ጋር 10 ቢሊዮን ዩሮ ለማበደር ተስማምተው ነበር ። በቅድመ ግዴታው መሠረት የኒቆስያ መንግሥት ከሃገር ውስጥ 5.8 ቢሊዮን ዩሮ እንዲያሰባስብ ተጠይቋል ። ስለ ቆጵሮስ የገንዘብ ቀውስና መዘዞቹ የብራሰልሱን ዘጋቢያችንን ገበያው ንጉሴን በስልክ አነጋግረናል ።

ገበያው ንጉሴ

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ