1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የበርሊን ግንብ የፈረሰበት ሃያኛ አመት በፎቶ

ዓርብ፣ ጥቅምት 27 2002

የዛሬ ሃያ-አመት በርሊን ላይ የሆነዉ-ከመሆኑ በፊት ይሆናል ብሎ ማሰብ በርግጥ ሲበዛ ከባድ ነበር።ሆነ

https://p.dw.com/p/KQ4p
ግንቡምስል picture-alliance/ dpa
የበርሊን ግንብ የፈረሰበት ሃያኛ አመት በአል ጀርመን ዉስጥ በተለያዩ ሥነ-ሥርአቶች እየተከበረ ነዉ።የግንቡ መፍረስ የጀርመንን ብቻ ሳይሆን የመላዉ አለምን የእስከዚያ ዘመን ምጣኔ-ሐብታዊ፤ ወታደራዊ ፖለቲካዊ ሒደትን በሙሉ ነዉ የለወጠዉ። ከሰባ-ዘመናት በላይ የፀናዉ ኮሚንስታዊ ሥርዓት ከአለም ጨርሶ ባይወገድም ክፉኛ ተሸመድምዷል።በሌላ በኩል የካፒታሊስቱ ሥርዓት የበላይነት ተረጋግጧል።ከሁለተኛዉ የአለም ጦርነት ፍፃሜ በሕኋላ ኑክሌር ያማዝዛል ተብሎ ሲፈራ የነበረዉ የቀዝቃዛዉ ጦርነትም ከበርሊን ግንብ ጋር አክትሟል። የዛሬ ሃያ-አመት በርሊን ላይ የሆነዉ-ከመሆኑ በፊት ይሆናል ብሎ ማሰብ በርግጥ ሲበዛ ከባድ ነበር።ሆነ።የበርሊን ግንብ ፍፃሜ ለአለም የአዲስ ዘመን-አዲስ ስርዓት ብርቀት ነዉ።ከዚያ ለመድረስ ግን ዓለም በርግጥ ብዙ መስዋዕትነት፥ የዘመናት ፖለቲካዊ-ዲፕሎማሲያዊ ሽኩቻ፥ ወታደራዊ ፍጥጫ፥ እና ሌሎች ብዙ መሰናክሎችን ማለፍ ግድ ነበረበት።ብቻ ዘንድሮ-ሃያ አመቱ። ይናገራል ፎቶ----