1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቡሩንዲ ሬፈረንደም

ሐሙስ፣ ግንቦት 9 2010

በቡሩንዲ ፕሬዚደንት ፒየር ንኩሩንዚዛ እንደገና ለር/ብሔርነት እንዲወዳደሩ ሲባል በሕገ መንግሥቱ ላይ በቀረበው ማሻሻያ ላይ በዛሬው ዕለት ውሳኔ ሕዝብ እየተካሄደ ነው። ውሳኔ ሕዝቡ ከጎርጎሪዮሳዊው 2005 ጀምሮ ሀገሪቱን በመምራት ላይ ያሉት ንኩሩንዚዛ ለተጨማሪ የስልጣን ዘመን እንደሚወዳደሩ ካስታወቁ ከሶስት ዓመት በኋላ ነው የተካሄደው።

https://p.dw.com/p/2xtUq
Burundi Verfassungsreferendum
ምስል DW/A. Niragira

የንኩሩንዚዛ ውሳኔ ያኔ ሀገሪቱን እከፋ የፖለቲካ ቀውስ ላይ መጣሉ ሲታወስ፣ በቀውሱ ሰበብ 1,200 ሰዎች ሲገደሉ፣ ከ400,000 የሚበልጡ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። የቡሩንዲ ተቃዋሚ ቡድኖች ሕዝቡ ከሬፈረንደሙ እንዲርቅ ጥሪ አስተላልፈዋል። ውሳኔ ሕዝብ በቡሩንዲ ውጥረቱ ይበልጡን እንዲካረር አድርጓል።

አርያም ተክሌ/አፖሊኔር ኒዪሮራ

ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ