1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የባህር ላይ ውንብድናን አስመልክቶ በዱባይ የተከፈተው ጉባኤ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 11 2003

ለባህር ላይ ውንብድና አስመልክቶ ያለው መፍትሄ ለማፈላለግ ከ50 አገሮች የተውጣጡ የሀገር አስተዳደር ሚኒስትሮችና የኢንዱስትሪ ሐላፊዎች፤ ለሁለት ቀናት ዱባይ ላይ እየመከሩ ነው።

https://p.dw.com/p/RJ2D
ምስል picture alliance/Photoshot

ሰኞ ዕለት የተከፈተው ይሄው ጉባኤ፤ የባህር ላይ ውንብድና የደቀነውን ችግር በዓለም አቀፉ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ፤ ማጉላት እንዳለበት፤ በሐምቡርግ ከተማ የሚገኘው «የጀርመን የንግድ መርከቦች ማህበር» ቃል አቀባይ ማክስ ጆንስ ለጆቼ ቬለ አስረድተዋል። በዱባይ ጉባኤ ላይ የተገኙት የሱማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር፤ ሞሀመድ አብዱላሂ ኦማር፤ የባህር ላይ ውንብድናን ለመታገል ይቻል ዘንድ፤ በሱማሊያ ሁኔታዎች መረጋጋይ ይኖርባቸዋል፤ ለዚህም የውጭ ሀገራት እርዳታ አስፈላጊ እንደሚሆን ገልፀዋል። «የጀርመን የንግድ መርከቦች ማህበር» ቃል አቀባይ ማክስ ጆንስ ከጉባኤው የሚጠብቁትን ከዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ነጋሽ መሐመድ