የባለራዕይ ወጣቶች አመራር መታሠር23 ግንቦት 2005ዓርብ፣ ግንቦት 23 2005የባለ ራዕይ ወጣቶች ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት እና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርታችኋል በሚል በፖሊስ ታሰሮ ምርመራ እንደተደረገበትና ፍርድ ቤትም እንደቀረበ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።https://p.dw.com/p/18i3Yምስል APማስታወቂያ ወጣቱ መጀመሪያ የታሰረዉ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚቀጥለዉ እሁድ ለጠራዉ ሰላማዊ ሰልፍ ታስተባብራለህ በሚል ነበር። ሆኖም ክሱ አቅጣጫዉን ስቶ ለግንቦት ሰባት ቅስቀሳ ታካሂዳለህ በሚል ምርመራ እየተካሄደበት እንደሆነ የድርጅቱ ፕሬዝደንት ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል። ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ዝርዝሩን ልኮልናል፤ ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ሸዋዬ ለገሠ ሂሩት መለሰ