አርባ-አራተኛዉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳት ባራክ ሁሴይን ኦባማ ዛሬ የመጀመሪያዉን የሙሉ ቀን ሥራቸዉን ጀምረዋል።ፕሬዝዳት ኦባማ ትናንት በአለ-ሲመታቸዉ ሲበከበር ያስተላለፉት መልዕክት ዛሬም መላዉ አለምን እያነጋገረ ነዉ።የኦባማ በአለ-ሲመትን ለማክበር ዋሽንግተን የታደመዉ ሕዝብ በአሜሪካ ታሪክ ታይቶ አይታወቅም።ወኪላችን አበበ ፈለቀ እንደዘገበዉ በበአሉ ላይ ወደ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ተገኝቶ ነበር።