1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የብሪታንያ ምርጫ ሒደት

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 28 2002

በምረጡኝ ዘመቻ ወቅት በሰወስቱ ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች መካካል የጎላ የመርሕ ልዩነት ባለመታየቱ የተመዘገበዉ ሁሉ ድምፁን መስጠቱ ብዙ አጠራጥሯል።

https://p.dw.com/p/NGAQ
የሰወስቱ ፓርቲዎች መሪዎችምስል AP

የብሪታንያ ሕዝብ የወደፊት እንደራሴዎቹን ለመምረጥ ዛሬ ድምፁን እየሰጠ ነዉ። ስድስት መቶ ሐምሳ መቀመጫዎች ላሉት ለሐገሪቱ ምክር ቤት አራት ሺሕ ያሕል እጩዎች ይወዳደራሉ። ምርጫዉን በከፍተኛ የድምፅ ልዩነት ያሽንፋል ተብሎ የሚጠበቅ ፓርቲ ግን የለም። ድምፅ ለመስጠት ከአርባ አራት ሚሊዮን በላይ መራጭ ተመዝግቧል። ይሁንና በምረጡኝ ዘመቻ ወቅት በሰወስቱ ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች መካካል የጎላ የመርሕ ልዩነት ባለመታየቱ የተመዘገበዉ ሁሉ ድምፁን መስጠቱ ብዙ አጠራጥሯል።የለንደኑ ወኪላችን ድልነሳ ጌታነሕ እንደታዘበዉ እስከ ቀትር ድረስ ድምፁን ለመስጠት የወጣዉ ሕዝብ ቁጥርም አነስተኛ ነዉ። ድልነሳን በሥልክ አነጋግሬዋለሁ።

ድልነሳ ጌታነህ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ