1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቱርክ-ሶርያ ውዝግብና የኔቶ ውሳኔ

ማክሰኞ፣ ሰኔ 19 2004

ቱርክ ባለፈው ዓርብ አንድ የሀገርዋን ተዋጊ አይሮፕላን መታ በጣለችው በሶርያ አንጻር ወደፊት አጸፋ ርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ እንደማትል የቱርክ ጠቅላይ ሚንስትር ጠይብ ሬቼፕ ኤርዶኻን ከሀገራቸው ምክር ቤት ጋ ባደረጉት ምክክር አስጠነቀቁ።

https://p.dw.com/p/15Ldp
ARCHIV - Ein Kampfflugzeug vom Typ Phantom F4 der türkischen Luftwaffe landet am Donnerstag (24.06.2010) auf dem Fliegerhorst Lagerlechfeld (Schwaben) mit Bremsfallschirm. Das syrische Militär hat in der Nacht zum Samstag 23.06.2012 bestätigt, dass ein türkisches Kampfflugzeug vor der Küste über dem Meer abgeschossen wurde. Die Maschine sei mit hoher Geschwindigkeit und in niedriger Flughöhe in syrischen Luftraum eingedrungen, hieß es. Türkische und syrische Marineeinheiten suchten inzwischen gemeinsam nach den beiden vermissten Besatzungsmitgliedern des Jets vom veralteten Typ F4-Phantom. Foto: Stefan Puchner dpa/lby +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

በሶርያ ወቀሳ አንጻር፣ "ኤፍ 4 ፋንቶም " የተባለው የቱርክ ተዋጊ አይሮፕላን ተመቶ በወደቀበት ጊዜ በሶርያ የበረራ ክልል ውስጥ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ክልል ውስጥ እንደነበረ ነው ቱርክ ያስታወቀችው። ቱርክ አባል የሆነችበት የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ኪዳን ኔቶ የሶርያን ርምጃ ተቀባይነት የሌለው ሲል በጥብቅ አውግዞታል።


በቱርክ ጥሪ መሠረት ኔቶ ሶርያ የቱርክ ተዋጊ አይሮፕላንን መታ በጣለችለት ጉዳይ ላይ ዛሬ በልዩ ስብሰባ ከተወያየ በኋላ ድርጊቱን ማውገዙን የኪዳኑ ዋና ፀሐፊ ፎኽት አንደርስ ራስሙሰን አስታውቀዋል።
« ይህን ተግባር ተቀባይነት የሌላቸው አድርገን እናየዋለን። በመሆኑም በጥብቅ አውግዘነዋል። ይህ የሶርያ ባለሥልጣናት ዓለም አቀፍ ደንቦችን፡ ሰላምን እና ፀጥታን የሰው ሕይወት ደንታ እንደሌላቸው የሚያሳይ ተጨማሪ ምሳሌ ነው። »
ሀያ ስምንቱ አባል ሀገሮች የሚጠቃለሉበት ኔቶም ከቱርክ ጎን መቆሙን ራስሙሰን አክለው አረጋግጠዋል። ኔቶ በአንድ አባል ሀገር ጥሪ መሠረት ምክክር ለማድረግ ልዩ ስብሰባ ሲጠራ ይህ ሁለተኛው ጊዜ ነው። እአአ በ 2003 ዓም የኢራቅ ጦርነት ሊካሄድ ጥቂት ጊዜ ሲቀረው ቱርክ የድንበርዋን ጥበቃ ለማረጋገጥ የኔቶን ድጋፍ በጠየቀችበት ጊዜ ነበር ኔቶ የመጀመሪያውን ልዩ ስብሰባ የጠራው።
የአውሮጳ ህብረትም ሶርያ የአየር ክልሏን ጥሶ ገብቶዋል በሚል የቱርክ ተዋጊ አይሮፕላንን መታ በምሥራቃዊ ሜድትሬንያን ባህር የጣለችበትን ድርጊት አውግዞታል።
አይሮፕላኑ ተመቶ በወደቀበት ጊዜ የምሥራቃዊ ሜድትሬንያን ባህር የተተከሉ ራዳሮቹን በመፈተሽ የስልጠና በረራ ላይ ነበር።
የቱርክ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ቢውለንት አርኒች ሀገራቸው ጦርነት ፈላጊ አለመሆንዋን ቢገልጹም፡ የሶርያ ርምጃ ካለምላሽ እንደማይቀር ዝተዋል።
« ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት መደረግ ያለበት ሁሉ ይደረጋል። ግን ጦርነት የማወጅ ዓላማ የለንም። »

ይህ በዚህ እንዳለ፡ ሁለት በሶርያ ተመቶ የወደቀው አይሮፕላን አብራሪዎችዋን ፍለጋ ያሰማራችው ሌላ ሁለተኛ አይሮፕላንዋም እንደተመታባት ቢውለንት አርኒች አክለው አስታውቀዋል።
« የነፍስ አድን ቡድኖችን የያዘ አንድ " ካዛ" የተባለ አይሮፕላን፣ የጠፉትን ሁለት አብራሪዎች ፍለጋ በተሰማራበት ጊዜ ከመሬት በኩል ጥቃት ተሰንዝሮበታል። በዚሁ ጊዜ ከሶርያ መንግሥት ጋ ግንኙነት በማድረጋችን ጥቃቱ ሊቆም ችሎዋል። »
ፍለጋው ቢቀጥልም አብራሪዎቹ በሕይወት መገኘታቸው አጠራጣሪ መሆኑን የቱርክ መንግሥት አስታውቆዋል። ቀደም ሲል ቱርክ ለተመድ ፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በላከችው ደብዳቤ የሶርያ ፀብ አጫሪ ርምጃ የቱርክን ብሄራዊ ፀጥታ ብቻ ሳይሆን ላካባቢው ሰላምና ፀጥታም አሳሳቢ ስጋት መሆኑን ገልጾዋል።
አርያም ተክሌ
ተክሌ የኋላ

NATO Secretary General Anders Fogh Rasmussen briefs the media after a meeting of the North Atlantic Council at the Alliance headquarters in Brussels June 26, 2012. NATO member states condemned Syria on Tuesday for its shooting down of a Turkish military jet, calling it "unacceptable" and demanding that Damascus take steps to prevent further incidents. REUTERS/Francois Lenoir (BELGIUM - Tags: POLITICS MILITARY)
የኔቶ ዋ/ፀሐፊ ፎኽት አንደርስ ራስሙሰንምስል Reuters
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ