1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የታህሳስ ወር ሃገራዊ እና ባህላዊ ትርጓሜ ክፍል ሁለት

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 16 2007

መፀዉ ወይም መኽር ወር፤ ከመስከረም ሃያ ስድስት እስከ ታህሳስ ሃያ አምስት ይዘልቃል፤ ከታህሳስ ሃያ ስድስት ደግሞ በጋ ይጀምርና እስከ መጋቢት ሃያ አምስት ይዘልቃል። በዚህም ኢትዮጵያዉያን የገና በዓልን የሚያከብሩት ታህሳስ መጨረሻ በበጋ ወርራት ዉስጥ ነዉ።

https://p.dw.com/p/1EA4a

የታህሳስ ወር ሃገራዊ እና ባህላዊ ትርጓሜ በሚል ርዕስ በተለይ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በገበሬዉ ዘንድ ስለሚከናወኑ ተግባራትና ስለሚነገሩ ስነ- ቃሎች ባለፈዉ ሳምንት ባቀረብነዉ የመጀመርያ ክፍል ዝግጅት መምህር ካሳይ ገብረ እግዚአብሄርና፤ ሊቀ-ኽሩያን በላይ መኮንን፤ ሰፊ ማብራርያ እንደሰጡን ይታወሳል። በዕለቱ ዝግጅታችን በመፀዉ ወይም መኸር ወቅት በተለይም በኢትዮጵያ ሰብል በሚሰበሰበት በታህሳስ ወር በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የገበሬዉን ህይወት የሚያስቃኙንን ሥነ-ቃሎችና ወጎች እናያለን።