የታክሲ ዉስጥ ፅሁፎች
ዓርብ፣ መጋቢት 14 2004ማስታወቂያ
ላጭር ጊዜ ወደ አንድ አግጣጫ ከመጓዝ ባለፍ-ምንም የማይታዋወቁ መንገደኞች ባንድ አሳፍሮ ፊት-ለፊት አስቀምጦ የግድ ያሕል ለንግግር፥ ለወሬ፥ ለለከፋ፥ አንዳዴም ለተረብ፥ ጠብ በመጋበዙ ከመጓጓዣ-ታክሲነቱ ይልቅ አነጋጋሪነቱ አመዝኖ ዉይይት መጠሪያዉ ሆኖ ቀርቷል።ድሮ ጋሪ ፈረስ ላይ የደረሰዉ በሱም ደርሶ ከትላልቅ ከተሞች እያረቀ፥ ከገበያም እየወጣ ዘመኑ ያለፈበት ዉይይትን የተኩት ዘመነኛ ታክሲዮች እንደ ዉይይቱ በቃል-አላወያይ ብለዉ ነዉ መሰል በፅሑፍ ይዥጎረጎሩ ይዘዋል።ፅሁፉ ባብዛኛዉ አጫጭር ግን ቅይጥ ነዉ፥መልዕክቱም ብዙ።ሥነ-ልቡናዊ፥ ማሕበራዊ፥ ፖለቲካዊ፥ ሐይማኖታዊ እና ሌላም።ፅሁፉ ታኪሲና ብጤዎቹን ሙጥኝ ማለቱ ግን፥ የድሬዳዋዉ ወኪላችን ዩሐንስ ገብረ-እግዚ አብሔር እንደሚያወጋን፥ የባሕል፥የእምነት፥የፖለቲካ ጫና በአደባባይ የመናገር መብት-ድፍረትን ማገዳቸዉን ጠቋሚ ነዉ።
ዩሐንስ ገብረ-እግዚ አብሔር
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሰ