1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የታይላንድ ጠቅላይ ሚንስትር ሥንብትና ተቃዋሚዎች

ማክሰኞ፣ ኅዳር 23 2001

ለሕዝብ አመፅ፥ ግፊት፥ ለፍርድ ቤት ብይን ለመገዛት ግን ...

https://p.dw.com/p/G7fP
ስልፈኛዉምስል AP

የታይላድ ጠቅላይ ሚንስትር ሶምቻይ ዎንግሳዋት የሐገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሥልጣን እንዲለቁ ያሳለፈባቸዉን ብይን ተቀበሉት።ፍርድ ቤቱ በምርጫ ማጭበርበር የተወነጀለዉ የጠቅላይ ሚንስትር ሶምቻይ የፖለቲካ ማሕበር እንዲታገድም በይኗል።የጠቅላይ ሚንስትር ሶምቻይ መንግሥት ሥልጣን እንዲለቅ ለማስገደድ ላለፈዉ አንድ ወር ሕዝባዊ ሠልፍ እና እና አድማ ሲያደራጅ የነበረዉ ተቃዋሚ ፓርቲ የፍርድ ቤቱን ብይን በደስታ ነዉ የተቀበለዉ።ነጋሽ መሐመድ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።