1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቻይና ድርጅቶች እና የአፍሪቃውያን ትችት

ሰኞ፣ ግንቦት 27 2004

አፍሪቃ ውስጥ በቻይናውያን ላይ በርካታ ትችቶች ይሰማሉ። የተፈጭሮ ሀብታችንን ይበዘብዛሉ፣ የስራ ቦታችንን ይሻሙብናል፣ ለሚቀጥሯቸው ሰራተኞች በደንብ አይከፍሉም። ሌላም ሌላም። በርግጥ ይህ እውነት ነውን? ቻይናውያን ለአህጉሯ መጥፎ ይሆኑ?

https://p.dw.com/p/157s7
Senegalese shop assistants wait for clients under the watch of the Chinese owner's sister at a street-side shop in Dakar, Senegal, June 28, 2007. Market stalls are just one of the most visible signs of China's massive penetration into African economies. The Asian giant _ a ready buyer of oil and other raw materials for more than a decade _ is also a major bidder on construction projects, a multi-million-dollar lender and a growing player in Africa's telecommunications and textile industries. (ddp images/AP Photo/Rebecca Blackwell)
ምስል REBECCA BLACKWELL/AP/dapd

ቻይናውያን በአፍሪቃ እዚሁ ቦን አቅራቢያ በኮሌኝ ከተማ በተኪያሄደ ስብሰባ ላይ የአፍሪቃ የኢኮኖሚ ተንታኞች ካነሱት ርዕስ አንዱ ነው። ቻይናውያን በአሉታዊ መንገድ ብቻ ሳይሁን በአዎንታዊ ጎንም ሳይነሱ አላለፈም።

ኢስማሌል ምሪሾ ከቻይናውያን ጋ የነበረው ተሞክሮ ጥሩ ነው። ታንዛናዊው ወጣት ላለፉት 7 ዓመታት ነጭ ሽንኩርት ከቻይና በማስገባት ወደ ሌሎች የአፍሪቃ አገሮች ለሚሸጥ አንድ ትንሽ ድርጅት ይሰራል። ምሪሾ አብሯቸው ስለሚሰራ ቻይናውያን ለጓደኞቹ ሲነግር ግን የሚሰማው ወቀሳ ብቻ ነው። የራሳችንን ነጭ ሽንኩርት እንዳንሸጥ ቻይናውያን አቅራቢ ይሆናሉ የመሳሰሉ ወቀሳዎችን ይሰማል። የምሪሾ እይታ ግን ከዚህ ይለያል። የቻይና ነጭ ሽንኩርት ፍሬዎች ከታንዛኒያዎቹ ጋ ሲነፃፀሩ ትላልቅ ናቸው። ስለሆነም ሰው ይመርጣቸዋል። ታንዛናዊያን ይህንን ፍላጎት ማሟላት ላልቻሉ የራሳቸው ጥፋት ነው ባይ ነው።

« በርካታ አፍሪቃውያን የቻይናውያን ፀባይን እና የስራ አመራር ይወቅሳሉ። ለኛ ለአፍሪቃውያን ደንታ እና ከበሬታ የላቸውም ይላሉ። እኔ በበኩሌ አለቃዬ በጣም ጥሩ ሰው ነው። አልፎ አልፎ አብረን ወጣ እንላለን። ጥሩ ይከፍለኛል። ሊረዳኝም ይሞክራል። ከሌሎች ግን እውነቱን ለመናገር የምሰማው ተቃራነውን ነው። ቻይናውያን እዚህ የሚመጡት ትርፋማ ለመሆን እና ተመልሰው ወደ አገራቸው መሄድ እንደሚፈልጉ ብቻ ነው።»

Titel: Die chinesische Wissenschaftlerin Katy Lam Schlagworte: China, Afrika, Migration, Diskriminierung Wer hat das Bild gemacht?: Adrian Kriesch Wann wurde das Bild gemacht?: 31.5.2012 Wo wurde das Bild aufgenommen?: Tagung der Vereinigung für Afrikawissenschaften in Köln Bildbeschreibung: Bei welcher Gelegenheit / in welcher Situation wurde das Bild aufgenommen? Wer oder was ist auf dem Bild zu sehen? Die chinesische Wissenschaftlerin Katy Lam von der Universität Lausanne in der Schweiz bei der Tagung der Vereinigung für Afrikawissenschaften in Köln In welchem Zusammenhang soll das Bild/sollen die Bilder verwendet werden?: Artikel
ኬቲ ላምምስል DW

ከሲውዘርላንድ ዮንቨርሲቲ የመጡት የኢኮኖሚ ምሁር ኬቲ ላምም ይህንን ነው የሚያረጋግጡት። ጋና እና ቤኒን ውስጥ ባለሙያዋ ለበርካታ ወራት ከቻይናውያን እና የአገሬው ህብረተሰብ ጋ ተወያይተዋል።

«በርካቶች በአፍሪቃ ያሉት ቻይናውያንን የቻይና መንግስት የላካቸው ነው የሚመስላቸው።ነገር ግን ይህ ልክ አይደለም። ከመንግስታቸው ድጋፍ እንኳን አያገኙም። በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ ናቸው። ሁኔታው እንደማንኛውም ወደ ሌላ ቦታ የሚሄድ የውጭ አገር ዜጋ ለነሱም ቀላል አይደለም። ብዙ ጊዜ በቋንቋ ችግር የተነሳ ከአገሩ የአኗኗር ስልት ጋ መላመድ የሚያቅታቸው ይመስለኛል።»

በተለይ የቻይና ድርጅቶች አፍሪቃ ውስጥ እክል ይገጥማቸዋል። በነሱ ላይ የሚሰማው ወቀሳ በአንዳንድ የአፍሪቃ አገሮች የፖለቲካ ማራመጃ ሆኗል ይላሉ ካቲ ላም። የምርጫ ዘመቻ ሰሞን የቻይናውያን ጥላቻ የሚገልፁ ድምፆች በአንዳንድ የአፍሪቃ አገሮች መታዘባቸውን ያስረዳሉ። «በቤኒን 40 የጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች ነበሩ አሁን ግን ሶስት ብቻ ናቸው የቀሩት፤ ሌሎቹ ፍቃዳቸውን ተነጥቀዋል» ይላሉ ላም። እንደ ሎሬንስ ማርፌኒግ አመለካከት አትራፊዎቹ ቻይናውያን ብቻ ሳይሆኑ አፍሪቃውያንም ናቸው። ማርፌኒግ ጀርመን የሚገኝ GIGA የተሰኘ የጥናት ተቋም ሰራተኛ ናቸው። በሴኔጋል እና ጋና ከትናንሽ ቻይናውያን ነጋዴዎች ጋ ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ይሞክራሉ። ቻይናውያን የጎዳና ተዳዳሪዎችን ቀጥረው በማሰራት በርካታ አፍሪቃውያን ወደ አውሮፓ እንዳይሰደዱ እድል ሰቷል ሲሉ ይገልፃሉ።

** FILE ** An unidentified man walks past a Chinese trader in Lagos, Nigeria, in this Aug. 1, 2002 file photo. Business and political leaders in Cape Town, South Africa, Friday June 15, 2007, attending an annual conference meant to focus entrepreneurial attention on Africa hailed China' and India's' huge appetite for raw materials as a powerful driving force to move the African economy up a gear.(ddp images/AP Photo/George Osodi)
ምስል GEORGE OSODI/AP/dapd

« ከጥቂት አመታት በፊት ለስደት የተዘጋጁ እጩዎች ነበሩ። ለእነሱ ከቻይናውያን ጋ ተባብረው በመስራት እድል ተከፍቶላቸዋል።አገር ጥለው ሳይሰደዱ በዚህ አጋጣሚ ገንዘብ ለማፍራት እና ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት ችለዋል። ዳካር ወይንም ጋና ውስጥ ስለ ቻይናውያን ወቀሳ ከተሰማ በብዛት ነጋዴዎች ናቸው። ግን አዎ ቻይናውያን ስራ ይሰጡናል ገንዘብ ለማፍራትም እድል ይከፍቱልናል። »

በአፍሪቃ ያሉ የቻይናውያን ገፅታ በተናጥል መመልከት እንደሚገባ የኢኮኖሚ ምሁሮቹ ይስማማሉ። በርግጥ መጥፎ ነገሮች ሲከሰቱም ይታያል። ከቻይና በሚገቡ ርካሽ ጫማዎች ሽያጭ የተነሳ ሴኔጋል ውስጥ 17 የተዘጉ የጫማ ፋብሪካዎች ማርፌኒግ ቆጥረዋል። ይሁንና እንደ ኢስማሌል ምሪሾ ያሉ አትራፊዎች እንዳሉም ልንዘነጋ አይገባም ሱሉ ያሳስባሉ።

አድሪያን ክሪሽ

ልደት አበበ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ