የኑሮ ውድነትና ብልሐቱ በድሬዳዋ
ዓርብ፣ ሐምሌ 3 2001ማስታወቂያ
ለዓለም አቀፉ የፋይናንስ ቀውስ ፣ መላ ፍለጋ፣ በኢንዱስትሪ የገሠገሡት መንግሥታት መምከር መዝከር ከጀመሩ ወራት አልፈዋል። የሰሞኑ የላአኩዊላው ጉባዔም፣ ትኩረቱ ፣ ከዚህ የተለየ አይደለም። የበለጸጉትን አገሮች ቆንጠጥ ያደረገው የኤኮኖሚ ጫና ፣ በችግር ማጥ ውስጥ የሚገኙትን አዳጊ አገሮችን ይበልጥ መጎነጡ የታወቀ ነው። የኢንዱስትሪ ምርት ብቻ ሳይሆን ዕለታዊ ምግብ በማነሱም ሆነ በመታጣቱ፣ የኑሮ ውድነት እንኳን ያጣ የነጣውን ፣ መለስተኛ ገቢ ያለውንም ሁሉ ማስጨነቁ አልቀረም።
ስለሆነም በሰፊው ቁጠባ በማድረግ ኑሮን ለመግፋት መጣር የግድ ነው። የኑሮ ውድነት በድሬዳዋ፣ ምን እንዳስከተለ ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር አንድ ዘገባም ሆነ ታሪክ አለው።
ዩሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ተክሌ የኋላ
ነጋሽ መሐመድ
►◄