1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአቶ መለስ ዜናዊ ዉርስና ቅርስ

እሑድ፣ ነሐሴ 24 2007

ከግንቦት 1983 ዓ.ም. አንስቶ ለቀጣይ 21 ዓመታት ኢትዮጵያን የመሩት የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሦስተኛ የሙት ዓመት ታስቧል። የሙት ዓመታቸዉን ለመዘከርም የተለያዩ ዝግጅቶች መከናወናቸዉ ተሰምቷል።

https://p.dw.com/p/1GNf4
Meles Zenawi Ministerpräsident Äthiopien
ምስል AP

የአቶ መለስ ዜናዊ ዉርስና ቅርስ

የሀገር ዉስጥ መገናኛ ብዙሃን እንደሚሉት የቀየሷቸዉ በተለይም የልማት እና የምጣኔ ሃብት መርሆዎችን ስልጣን ላይ የሚገኘዉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ተግባራዊ ለማድረግ እየሠራ ነዉ። ባለስልጣናቱም የእሳቸዉን ዉርስ እና ቅርስ ለማስቀጠል ቃል ሲገቡ ይደመጣል። ለመሆኑ አቶ መለስ በምን ይታወሳሉ? ዉርሳቸዉስ? ዝርዝሩን ከድምጽ ዘገባዉ ያድምጡ።

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ