የአዉሮጳ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ
ዓርብ፣ የካቲት 6 2007ማስታወቂያ
የዩክሬን ተፋላሚ ሐይላትና የየተፋላሚዎቹ ደጋፊዎች ትናንት ሚኒስክ-ቤላሩስ ዉስጥ የተፈራረሙት የሠላም ዉል ገቢራዊነቱ ብዙ እያነጋገረ ነዉ።ትናንትናዉኑ ብራስልስ-ቤልጅግ ተሰብሰበዉ የነበሩት የአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት መሪዎች ለስምምነቱ መፈረም የጣሩትን የጀርመንና የፈረንሳይ አቻዎቻቸዉን አንድንቀዉ ሥምምነቱን አወድሰዉታል።መሪዎቹ ከዚሕም በተጨማሪ ሥለግሪክ የምጣኔ ሐብት ቀዉስ፤ በተጠርጣሪ አሸባሪዎች ላይ መንግሥታቱ ሥለሚያደርጉት ቁጥጥርም ተነጋግረዉ።አዉሮጳ መድረሻ ሜድትራንያን ባሕር ዉስጥ የሚረግፉት የአፍሪቃዉያን ስደተኞች እልቂት ግን በሕብረቱ መሪዎች ዘንድ ከቁብ አልተቆጠረም።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ አጭር ዘገባ አለዉ።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ