1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮፓ ህብረት ና ዚምባብዌ

ረቡዕ፣ መጋቢት 18 2005

በውሳኔው መሰረት በ81 ግለሰቦችና በ8 ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው የንግድና የጉዞ እገዳ ተነስቷል ። የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤን ጨምሮ 10 ግለሰቦችና 2 ኩባንያዎች ግን አህንም እገዳው እንደፀናባቸው ይቆያል ።

https://p.dw.com/p/185A4
Collecting Watter in Glen Norah. Copyright: DW/Columbus Mavhunga, März 2013, Zimbabwe
ምስል DW/C. Mavhunga

የአውሮፓ ህብረት በዚምባብዌ ላይ ጥሎት የነበረውን የኤኮኖሚና የጉዞ እገዳ ከትናንት ጀምሮ በአብዛኛው ያነሳ መሆኑን የህብረቱ የውጭ ግንኙነት ሃላፊ ካትሪን አሽተን አስታውቀዋል ። ውሳኔው የተላለፈው በቅርቡ በዚምባብዌ የተካሄደው ህገ መንግሥታዊ ህዝበ ውሳኔ ሠላማዊና ተአማኒ መሆኑን ተክትሎ እንደሆነ ካትሪን አሽተን ያወጡት መግለጫ ያስረዳል ። በውሳኔው መሰረት በ81 ግለሰቦችና በ8 ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው የንግድና የጉዞ እገዳ ተነስቷል ። የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤን ጨምሮ 10 ግለሰቦችና 2 ኩባንያዎች ግን አህንም እገዳው እንደፀናባቸው ይቆያል ። ገበያው ንጉሴ ከብራስለስ ዝርዝር ዘገባ አለው ።
ገበያው ንጉሴ
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ