1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮፓ ህብረት እርዳታ ለአሚሶም

ረቡዕ፣ መስከረም 16 2005

ይኽው ተጨማሪ እርዳታ አሚሶም ተልዕኮውን በሙሉ አቅሙ እንዲወጣ የሚያግዝ መሆኑን የአውሮፓ ህብረት ገልጿል ። ፣ህብረቱ ተጨማሪ እርዳታ የሰጠው የአሚሶም የእስካሁኑ ተግባር አበረታች በመሆኑ ምክንያት ነው ሲሉ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኑነቶች ቢሮ ቃል አቀባይ ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።

https://p.dw.com/p/16Fam
In this photo taken Monday, April 30, 2012 and released by the African Union-United Nations Information Support Team Tuesday, May 1, 2012, Ugandan soldiers of 341 Battalion serving with the African Union Mission in Somalia (AMISOM) man the frontline near the main road on the northern edge of Maslah Town, the northern city limit of the Somali capital Mogadishu, in Somalia. (Foto:AU-UN IST, Stuart Price/AP/dapd).
ምስል AP
የአውሮፓ ህብረት በሶማሊያ የአፍሪቃ ህብረት ሰላም አስከባሪ አሚሶምን ለማገዝ ተጨማሪ 82 ሚሊዮን ዩሮ ለመስጠት መወሰኑን ትናንት አስታውቋል ። ይኽው ተጨማሪ እርዳታ አሚሶም ተልዕኮውን በሙሉ አቅሙ እንዲወጣ የሚያግዝ መሆኑን የአውሮፓ ህብረት ገልጿል ። ፣ህብረቱ ተጨማሪ እርዳታ የሰጠው ሶማሊያ ዘላቂ ሰላም እንዲኖራትና እንድትረጋጋ በሚደረገው ጥረት ወሳኝ ሚና የሚጫወተው የአሚሶም የእስካሁኑ ተግባር አበረታች በመሆኑ ምክንያት ነው ሲሉ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኑነቶች ቢሮ ቃል አቀባይ ለዶቼቬለ ተናግረዋል ። የብራሰልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴ ዝርዝር ዘገባ አለው ።

ገበያው ንጉሴ

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሰ