1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ

ረቡዕ፣ ግንቦት 14 2005

የዛሬው የ27 ቱ አባል ሃገራት መሪዎች ጉባኤ ከመጀመሩ አስቀድሞ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦሎንድ እንደተናገሩት ጉባኤው በግለሰቦችም ሆነ በኩባንያዎች ደረጃ ለሚፈፀመው የታክስ ማጭበርበር እኩል ትኩረት ይሰጠዋል ።

https://p.dw.com/p/18cFH
ምስል Reuters


በከፍተኛም ሆነ በዝቅተኛ  ደረጃ የሚካሄደው የታክስ ማጭበርበር ዛሬ ብራሰልስ ቤልጂግ በመካሄድ ላይ ያለው የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት የመሪዎች ጉባኤ ትኩረት ነበር። በፈረንሳይና በጀርመን አንዳንድ ታዋቂ ግለሰቦች ቀረጥ እንዳይከፍሉ ገንዘባቸውን ወደ ሌሎች አገራት ማሸሻቸው በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ከተደረገ ወዲህ የታክስ ማጭበርበር በአሁኑ ጊዜ በአውሮፓም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት ስጥቷል። የዛሬው  የ27 ቱ አባል ሃገራት መሪዎች ጉባኤ ከመጀመሩ አስቀድሞ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦሎንድ እንደተናገሩት ጉባኤው በግለሰቦችም ሆነ በኩባንያዎች ደረጃ ለሚፈፀመው የታክስ ማጭበርበር እኩል ትኩረት ሰጥቶ ይነጋገራል። የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ኬምረን ደግሞ የሚጣለው የግብር ወይም የታክስ መጠን የንግድ ድርጅቶች ሥራ እንዲፈጥሩ የሚያበረታታ መሆን እንደሚገባው አሳስበዋል። ስለ ዛሬው የአውሮፓ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የመነጋገሪያ አጀንዳ የብራሰልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴ ዝርዝር ዘገባ አለው።
ገበያው ንጉሴ
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ