1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዲሱ የፓሪያርክ ምርጫ በኢትዮጵያ

ማክሰኞ፣ የካቲት 12 2005

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶሱ በወሰነው መሰረት የካቲት 21 የፓትሪያርክ ምርጫ ይካሄዳል። የካቲት 24 ደግሞ በአዕለ ሲመቱ ይከበራል።

https://p.dw.com/p/17hTv
ምስል DW

የምርጫው ሂደቱን በተመለከተ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን የህዝብ ግንኙት መምሪያ ሀላፊ የሆኑት- አቶ እስክንድር ገብረ ክርስቶስን ልደት አበበ አነጋግራቸዋለች። የአስመራጭ ኮሚቴው የደረሰበትን በመግለፅ አቶ እስክንድር ይጀምራሉ።

በትክክል ስለ 5ቱ የፓትሪያርክ እጩዎች ማንነት የሚታወቀው በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት የካቲት 16 መሆኑን አቶ እስክንድር ገልፀውልናል። ይህም የሚሆነው መላው የሲነዶስ አባላት በተገኙበት የአስመራጭ ኮሚቴው እጩ አድርጎ የተቀበላቸውን ሰዎች ይፋ ካደረገ በኋላ ነው። የ6ኛው ፓትሪያርክ ምርጫ በዕጣ ሳይሆን በድምፅ አሰጣጥ እንደሚሆን አቶ እስክንድር አስረድተዋል።

በመጨረሻ ለአቶ እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ያነሳሁላቸው ጥያቄ በሀይማኖቶች አባቶች መካከል የተጀመረው ዕርቅ ሳይጠናቀቅ ወደ አዲስ ፓትሪያርክ ምርጫ መሄዱ ለወደፊቱ የቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነት ምን አይነት ሚና እንደሚኖረው ነው።

ልደት አበበ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ