1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዲስ ሥነ ቴክኒክ ግኝቶች ባለቤት

ረቡዕ፣ ጥር 23 2004

ባለፈው ሳምንት ሳይንስና ኅብረተሰብ ቅንብራችን፣ በዩናይትድ እስቴትስ ከሚኖሩ

https://p.dw.com/p/13pq6
ምስል picture alliance/dpa

ኢትዮጵያዊ የፊዚክስ ፕሮፌሰር ጋር ባደረግነው ጭውውት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ፤ ተማሪዎች፤፣ ወጣቶች የሳይንስ ትምህርትን ይወዱ ዘንድ ስለማነቃቂያው መላ ፤ ጠይቀናቸው እንደነበረ ይታወስ ይሆናል። ለፕሮፌሰር ሰሎሞን ቢልልኝ ፣ ያን ጥያቄ ማቅረባችን፣ (ያቀረብነው)ሳይንስና ሥነ ቴክኒክ፤ ለታዳጊ አገሮች ዕድገትም ሆነ ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ ግምት ውስጥ በማስገባት ነበረ ። በዛሬው ዝግጅታችን እንሆ፤ ሳይንስን ፣ሥነ ቴክኒክን ወደው ፤ በአገር ውስጥና በውጭ ተምረው ከተመለሱ በኋላ፣ በአሁኑ ጊዜ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የሥነ-ቴክኒክ ተቋም ሙያዊ ትምህርት አቅራቢ(ሌክቸረር) በመሆን የሚያገለግሉትንና የፈጠራም ሆነ የምርምር አዲስ ግኝቶች ባለቤት በመሆን 2 ጠቃሚ ነገሮችን ለናሙና ሠርተው ያቀረቡትን አቶ ሙሉነህ ለማን አነጋግረናል። በቅድሚያ እማኝ ከሆኑት ባልደረቦቻቸው መካከል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ተሾመ ይርጉ-----

አቶ ሙሉነህ ለማ፤ እስቲ ለናሙና ስላቀረቧቸው የሥነ ቴክኒክ የምርምር ውጤቶችዎ ምንነትና አገልግሎት ዘርዘር አድረገው ያስረዱን----

ተክሌ የኋላ

ሸዋዬ ለገሰ