1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር የሙከራ ጉዞ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 28 2007

በአሁኑ ሙከራም ለህዝቡ የባቡር አጠቃቀም ትምሕርት እየተሰጠ ነው ። በትራንስፖርት ችግር የተማረሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ባቡሩ ችግራቸውን ያቃልላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል ።

https://p.dw.com/p/1FL5o
Straßenbahn in Addis Abeba
ምስል DW/Y. Gebreegziabher

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ህዝብን አሳፍሮ የሙከራ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው ። ባቡሩ ከተመረቀ በኋላ አግልግሎቱ የዘገየው ለባቡር ትራንስፖርቱ አስፈላጊ የሆኑ አቅርቦቶች እስኪሟሉ ድረስ እንደነበር የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ለዶቼቬለ ተናግረዋል በአሁኑ ጊዜ ከጥቃቅን ነገሮች በስተቀር ለባቡሩ የሚያስፈልጉ አቅርቦቶች በሙሉ መሟላታቸውን ሃላፊው አስታውቀዋል ። በአሁኑ ሙከራም ለተጠቃሚው ህዝብ የባቡር አጠቃቀም ትምሕርት እየተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል ። ዛሬ በተካሄደ የሙከራ ጉዞ ላይ የተገኘው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር ያነጋገራቸው በትራንስፖርት ችግር የተማረሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ባቡሩ ችግራቸውን ያቃልላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚዘብሔር

ኂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ