1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ያማረረው የኤሌክትሪክ መቋረጥ

ረቡዕ፣ ግንቦት 5 2007

ነዋሪዎች እንደሚሉት የኤሌክትሪክ መቋረጥ በዕለት ተዕለት ህይወታቸው፤ በንግድ እንዲሁም በምርት ሂደት ላይ አሉታዊ ጫና አሳድሮባቸዋል ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ ችግሩ በማሰራጫና በማከፋፈያ አቅም ውስንነት አንዲሁም በብልሽት ምክንያት መፈጠሩን ለዶቼቬለ አስታውቋል ።

https://p.dw.com/p/1FPKT
Äthiopien Solar
ምስል Stiftung Solarenergie



የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በተደጋጋሚና ለረዥም ሰዓታት አንዳንዴም ለቀናት በሚደርሰው የኤሌክትሪክ መቋረጥ መማረራቸውን አስታወቁ ። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት የኤሌክትሪክ መቋረጥ በዕለት ተዕለት ህይወታቸው፤ በንግድ እንዲሁም በምርት ሂደት ላይ አሉታዊ ጫና አሳድሮባቸዋል ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ ችግሩ በማሰራጫና በማከፋፈያ አቅም ውስንነት አንዲሁም በብልሽት ምክንያት መፈጠሩን ለዶቼቬለ አስታውቋል ። በበዙ ወጪም የማስፋፍትና የማሰራጫዎች የማሻሻል ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ድርጅቱ ገልጿል ። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር እርእሩን ልኮልናል ።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ