1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ

ሰኞ፣ ጥር 20 2005

ትናንት በአዲስ አበባ በተከፈተው ሀያኛውን የአፍሪቃ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተገኙት አፍሪቃውያን ርዕሳነ ብሔር እና መራሕያነ መንግሥት በተለያዩ የአህጉሩ ጉዳዮች ላይ ውይይታቸውን ዛሬም ቀጥለው ውለዋል።

https://p.dw.com/p/17T3m
Heads of the African States pose for a group picture in Addis Ababa, Ethiopia, Sunday, Jan, 27, 2013, during the African Union Conference. African leaders met in the Ethiopian capital Sunday for talks dominated by the conflict in Mali as well as lingering territorial issues between the two Sudans. The African Union says it will deploy a force in Mali, where French troops are helping the Malian army to push back Islamist extremists whose rebellion threatens to divide the West African nation. (Foto:AP/dapd)
ምስል AP

የተመድ ዋና ፀሐፊ ፓን ኪ ሙንም ጭምር የተሳተፉበት ጉባዔው በዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ፡ በማሊ፡ በጊኒ ቢሳው፡ በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ፡ በሶማልያ ፡ በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን መካከል ስለቀጠሉት ውዝግቦች በሰፊው መክሮዋል። የአፍሪቃ ለውጥ እና ህዳሴ የሚል ርዕስ በያዘው በዚሁ ጉባዔ ንግግር ያሰሙት የህብረቱ ኮሚሽን ፕሬዚደንት ንካኦሳዛና ድላሚኒ ዙማ አህጉሩን ቀስ በቀስ ወደ ውህደት ለማድረስ ለሚቻልበት አሰራር ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል። በሌላ በኩል ደግሞ በአፍሪቃ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተለያዩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች ተሰጥተዋል። በአህጉሩ ግጭት እየተካሄደባቸው የሚገኙ ማሊንና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ የመሳሰሉት ሀገራት ጉዳይ መግጫዎቹ ያተኮሩ ናቸው። በመግለጫዎቹ የተነሱትን ሀሳቦች ባጭሩ እንዲያብራራልን ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት ጠይቄው ነበር።

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ