1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ሠላምና ሠላም አስከባሪ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 21 2005

ዉሳኔዉ ሠሜናዊ ማሊን ይቆጣጠሩ የነበሩትን የሙስሊም እና የቱአሬግ አማፂያንን እስካሁን ከሚወጋዉ የፈረንሳይ ጦር አባላት የተወሰነዉን፥ የምዕራብ አፍሪቃ የምጣኔ ሐብት ማሕበረሰብ (ኤኮዋስ) አባል ሐገራትን፥ እና የቻድ ወታደሮችን ሰማያዊ መለዮ ከማልበስ፥ የዕዝ መዋቅሩን ና ወጪን ከመለወጥ ባለፍ አዲስ ብዙም አዲስ ጦር አይዘምትበትም

https://p.dw.com/p/18PFh
Members of the United Nations Security Council vote to tighten sanctions on North Korea at the United Nations Headquarters in New York, March 7, 2013. In response to North Korea's third nuclear test, the U.N. Security Council voted on Thursday to tighten financial restrictions on Pyongyang and crack down on its attempts to ship and receive banned cargo in breach of U.N. sanctions. REUTERS/Brendan McDermid (UNITED STATES - Tags: POLITICS)
የፀጥታዉ ም/ቤትምስል picture-alliance/ap



የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር እንደዛቱት ጦራቸዉን ከሶማሊያ ካስወጡ ሶማሊያ ዉስጥ የፈነጠቀዉ ሠላም ባይዳፈን-እንደሚጋረድ የፖለቲካ አዋቂዎች፣በሚያስጠነቅቁበት መሐል በድብቅ የሞቃዲሾ ኤምባሲያቸዉን የከፈቱት የብሪታንያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር በሶማሊያ አስተማማኝነት ሠላም የሚሰፍንበት ጊዜ መቃረቡን መሠከሩ።የብሪታንያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትርን መግለጫን የዓለም መገናኛ ዘዴዎች ሲቀባበሉት፤ የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት የማሊን ሠላም የሚያስከበር ሠራዊት ለማዝመት ወሰነ።ሐሙስ።በማግሥቱ፣ የአፍሪቃ እና የአዉሮጳ ሕብረቶች መሪዎች አፍሪቃ ዉስጥ ሠላም ለማስፈን ያደረጉት ጥረት ጥሩ ዉጤት ማግኘቱን አወደሱ።አዲስ አበባ፥ ሞቃዲሾ እና ኒዮርክ የተባለና የተወሰነዉን አስታከን የአፍሪቃን እዉነት ከሰላም ብያኔ እንዴትነት ጋር አጣቅሰን ባጭሩ እንቃኛለን።አብራችሁኝ ቆዩ።

የኢትዮጵያ መሪዎች የሶማሊያ ተቀናቃኝ ሐይላትን ለመሸምገል ከመጣር፣ መልፋት፣ መባተላቸዉ እኩል ሁለቱን ሱዳኖች ለማስታረቅ መዉጣት መዉረዳቸዉ እርግጥ ነዉ።ሶማሊያ ዉስጥ የወጣት ወታደሮቻቸዉን አካል፣ ደም፣ ሕይወትን ከመሰዋታቸዉ እኩል ከአብዬ እስከ ላይቤሪያ ሠላም አስከባሪ ወታደር ማዝመታቸዉ ሐቅ ነዉ።

የአዲስ አበባ መሪዎች በተደጋጋሚ እንዳሉት ሶማሊ እና ሥለ ሶማሊያ፣ ሁለቱ ሱዳኖች እና ሥለ ሁለቱ ሱዳኖች ያሉ ያደረጉትን ሁሉ የማለት ማድረጋቸዉ ምክንያት የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር፣ የጎረቤት ሐገራት ሕዝቦችን ለመርዳት ሊሆን ይችላል።

ወይም ተቃዋሚዎቻቸዉ እንደሚሉት በተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ በነፃ ጋዜጠኞች፣ በመብት ተሟጋቾች፣ በጥቅሉም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚፈፅሙትን አፈና እና ረገጣ ለመሸፈን ሊሆን ይችላል።ወይም ደግሞ ገለልተኛ ተንታኞች እንደሚሉት የአስመራ ጠላቶቻቸዉን በተዘዋዋሪ ጦርነት፣ ዲፕሎማሲ ለመምታት፣ የአፍሪቃ ቀንድ ልዕለ ሐይልነታቸዉን ለማስመስከር፣ አካባቢዉን ከዓረቦች በተለይም ከግብፆች ተፅዕኖ ለማላቀቅ ሊሆንም ይችላል።ഊ

ወይም ሌላ።አንድ ነገር ግን ሐቅ ነዉ።ያደረጉትን ሁሉ በማድረጋቸዉ የምዕራብ መንግሥታትን ሁለንተናዊ ድጋፍ ሸምተዉበታል።ዩጋንዳ፣ ብሩንዲና ኬንያ ጦራቸዉን ካዘመቱ ወዲሕ ግን አዲስ አበባና አዲስ አበባ ላይ ብቻ አተኩሮ የነበረዉ የዋሽግተን-ብራስልስ መሪዎች ቀልብ ወደ ካምፓላና ናይሮቢ መሳቡ አልቀረም።

ናይሮቢዎች ጦራቸዉን ሶማሊያ ባዘመቱ ማግሥት አዲስ አበቦች ጦራቸዉን ዳግም ማዝመታቸዉ በምዕራባዉያኑ ዘንድ እንደ ቀድሞዉ ብቸኛ ተፈላጊ ባያደርጋቸዉ እንኳ ከናይሮቢና ከካምፓላዎች አለማነሳቸዉን አስመስክሮላቸዋል።

ይሁንና አክራሪ፣ አሸባሪዉን ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብን ሞቃዲሾና ኪስማዩን ከመሳሰሉት ትላልቅ ሥልታዊ ከተሞችን የማስወጣቱን ዉለታ ከአዲስ አበባ ይልቅ ከአዲስ አበባ መሪዎች ብዙ ዘግይተዉ ጦር ያዘመቱት የካምፓላና የናይሮቢ መሪዎች መዉሰዳቸዉ አዲስ አበቦች ተፈላጊነታቸዉን ለማሳየት ሌላ እርምጃ እንዲያሰላስሉ ሳያስገድዳቸዉ አልቀረም።ጦራቸዉ ከሁዱር ማስወጣታቸዉ በግልፅ ከታዩት እርምጃዎች አንዱ ነዉ።

ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ ሽትራስ ቡርግ፣ ብራስልስና ፓሪስን በጎበኙ በሁለተኛዉ ሳምንት ምክር ቤት አባላት ፊት እንደዛቱት ሶማሊያ የሠፈረዉን ጦር ማሳወጣታቸዉ ብዙ የፖለቲካ ታዛቢዎች እንደሚሉት በብዙ ምክንያት አጠራጣሪ ነዉ።

ጠቅላይ ሚንስትሩ ያሉትን ማለታቸዉ ግን ከአዉሮጳ ሕብረት መሪዎች ጋር ባደረጉት ዉይይት የሚፈልጉትን አለማግኘታቸዉን ጠቋሚ፣ ወይም ተፈላጊነታቸዉን ለማሳየት ሌላ የተጠቀሙበት ሌላ ዘዴን አመልካች ነዉ።የኢትዮጵያ መሪዎች ሙከራ ከሽፎ፥ ወይም ወጪዉ አስገድዷቸዉ ጦራቸዉን ካስወጡ ግን በብራስልስ፥ ዋሽንግተኞች እንደታቀፉ ለመቆየት የሚቀራቸዉ ትልቅ ካርድ አንድ ብቻ ነዉ።ሱዳን።እንደዲፕሎማሲዉ ወግ ኢትዮጵያ ተባባሪ ወዳጅ ለሚባሉት ግን ደግሞ ተፈላጊነትን ለማትረፍ ኢትዮጵያን ለሚሻሙት ኬንያና ዩጋንዳን ለመሳሰሉት ሐገራት ረጨማሪ ሸከም ነዉ-የሚሆነዉ።ከሁሉም በላይ የምትከስረዉ ግን ለሃያ-ዘመናት ሠላም የማታዉቀዉ ለሶማሊያ ናት።

Mogadishu Somalis watch as Ethiopian troops on lorries make their way to the former American Embassy in Mogadishu, Somalia, Friday, Dec. 29, 2006. The leader of Somalia's Islamic political movement vowed Friday to continue the fight against Ethiopia, which lent key military support to the government in a campaign that saw the Islamic militia retreat from the capital a day earlier. (AP Photo/Mohamed Sheikh Nor)
ሶማሊያምስል AP
A picture taken on March 2, 2012 shows Ethiopian troops standing on an army tank at an air base in the city of Baido, which was taken over from Shebab rebels on February 22. Truckloads of Ethiopian and Somali troops on February 22 captured the strategic Somali city of Baidoa from Al-Qaeda-allied Shebab insurgents, who vowed to avenge their biggest loss in several months. Baidoa, 250 kilometres (155 miles) northwest of the capital Mogadishu, was the seat of Somalia's transitional parliament until the hardline Shebab captured it in 2009. Ethiopia says it is in the country to support Somalia?s transitional government to stamp out Shebab insurgents, but says it does not plan to remain in the country for the long term. AFP PHOTO / JENNY VAUGHAN (Photo credit should read JENNY VAUGHAN/AFP/Getty Images)
የኢትዮጵያ ጦር-ባደዎምስል JENNY VAUGHAN/AFP/Getty Images

የፀጥታ ጥናት ተቋም የፖለቲካ ተንታኝ አንድሩስ አሳሞሐ።የብሪታንያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ዊሊያም ሔግ በድብቅ ሶማሊያ ገብተዉ፥ በሞቃዲሾ የሐገራቸዉን ኤምባሲ የከፈቱት፥ ኢትዮጵያ ጦሯን ለማስወጣት የመዛቷን ሰበብ ምክንያትን፥ ዛቻዉ እዉን ከሆነ የሚያስከትለዉን መጥፎ ዉጤት እነ አሳሞሐ፥በሚተነትኑበት መሐል ነዉ።

ሔግ ሥለ ሶማሊያ የወደፊት ጉዞ የሚመክረዉን ዓለም አቀፍ ጉባኤ ለንደን ላይ ከማስተናገዳቸዉ ካንድ ሳምንት በፊት ለሃያ-ሁለት ዓመታት ተዘግቶ የነበረዉን የሞቃዲሾ ኤምባሲያቸዉን የከፈቱት መንግሥታቸዉና ተሻራኪዎቹ ለሶማሊያ ሠላም ተቆርቋሪ መስለዉ ለመታየት፥ ወይም ተቆርቋሪ መሆናቸዉን ከልብ ለማሳየት ሊሆን ይችላል።

ወይም ደግሞ ብዙዎች እንደሚያምኑት ከምዕራቡ ዓለም ጋር የምትወዛገበዉ ኢራን፥ በተዘዋዋሪ መንገድ የምትሻኮተዉ ቱርክ ሞቃዲሾ ዉስጥ ኤምባሲ በመክፈታቸዉ አዉሮጳ አሜሪካኖች ከሶማሊያ የሚፈልጉትን ጥቅም ላለመነጠቅ አልመዉ ሊሆን ይችላል።አላማ ምክንያቱ ምንም ሆነ ምን የብሪታንያዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ኤምባሲያቸዉን ሲከፍቱ ሥለ ሶማሊያ ሠላም ያሉት ግን የፖለቲካ ተንታኞቹ ካሉና ከሚሉት፥ ከሶማሊያም ተጨባጭ እዉነት የራቀ ነዉ።

«የቀድሞዉ ኤምባሲያችን ከተዘጋና ባንዲራዉ ከወረደ ከሃያ-ሁለት ዓመታት በሕዋላ ኤምባሲያችንን ሥንከፍት የመጀመሪያዉ ምዕራባዊ ሐገራት ነን።ይሕ እርምጃ ሶማሊያ በዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ እየታገዘች ችግሮቿን ማስወገድ እንደምትችል ለመተማመናችን አብነት ነዉ።ገቢራዊ ትብብራችንንም ያሳያል።»

ኤምባሲዉ ባንዲራ ከሚዉለበለብበት በስተቀር ዲፕሎማቶች የሉበት።ሥራ የሚጀምረዉ ሐምሌ ነዉ።ሐምሌም ሥራ ሲጀምር በደርሶ መልስ የሚሠራ እንጂ ሞቃዲሾ ዉስጥ በቋሚነት የሚሠራ አምባሳደር ወይም ዲፕሎማት አይመደብም።ሔግ በብረት ሰንዱቅ (ኮንተይነር) የተሠራ ባዶ ቤት ቁልፍ መክፈታቸዉ እንኳ የተነገረዉ ሞቃዲሾን ለቀዉ ከወጡ በኋላ ነዉ።

ይችን ሶማሌ ነዉ፥ የቀድሞዋ ሶማሊ ላንድ ቅኝ ገዢ፥ የአዉሮጳዋ ትልቅ ሐገር ትልቅ ዲፕሎማት ችግሯን ለማስወገድ እንደምትችል የሚተማመኑባት።የሔግ ድርጊት-ከቃላቸዉ፥ ቃላቸዉ ከሶማሊያ እዉነት መቃረኑ ምሥራቅ አፍሪቃ ላይ ሲያነጋግር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት የማሊን ሠላም የሚጠብቅ ሠራዊት እንዲሠፍር ወሰነ።

ዉሳኔዉ ሠሜናዊ ማሊን ይቆጣጠሩ የነበሩትን የሙስሊም እና የቱአሬግ አማፂያንን እስካሁን ከሚወጋዉ የፈረንሳይ ጦር አባላት የተወሰነዉን፥ የምዕራብ አፍሪቃ የምጣኔ ሐብት ማሕበረሰብ (ኤኮዋስ) አባል ሐገራትን፥ እና የቻድ ወታደሮችን ሰማያዊ መለዮ ከማልበስ፥ የዕዝ መዋቅሩን ና ወጪን ከመለወጥ ባለፍ አዲስ ብዙም አዲስ ጦር አይዘምትበትም።ተልዕኮዉ ግን እንደተናጋሪ፥ ተመልካቹ ለየቅል አንዳዴም ግራ አጋቢ ነዉ።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሠላም ማስከበር ተልዕኮ ሐላፊ ሔርቨ ላድሶዉ እንዳሉት ተልዕኮዉ ሠላም ማስከበር ብቻ ነዉ።

«የሠላም አስከባሪዉ ሐይል ተልዕኮ ፍፁም ግልፅ ነዉ።ፀረ-ሽብር ተልዕኮ አይደለም።የማረጋጋት ተልዕኮ እንጂ።በተልዕኮዉ የመጀሪያ ምዕራፍ የመጓጓዢያ ተሽከርካሪዎች፥ ድንኳኖች፥ የሐይል ማመንጫ (ጄኔሬተሮች) እና ሌሎች ለሲቢል አገልግሎት የሚዉሉ መሳሪያዎች ወደ ማሊ እንልካለን።»

የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ ባሳለፈዉ ዉሳኔዉ እንዳስታወቀዉ ግን የሚዘምተዉ ወይም የዘመተዉ ሠራዊት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከፈረንሳይ ወታደሮች ጋር ሆኖ የማሊ አማፂያንን ይወጋል።የሠራዊቱ ተልዕኮ ሠላም ማስከብር ከሆነ ማሊ ዉስጥ የሚከበር ሠላም አለ ማለት ነዉ።አማፂያኑን የሚወጋ ከሆነ ደግሞ ሠላም የለም ማለት ነዉ።

የማሊዉ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ቲመን ኮዉሊባሊ እንደሚሉት ደግሞ የሠራዊቱ ተልዕኮ ከተባለዉና ከሚባለዉ ሁሉ የላቀ ፈርጀ ብዙ ነዉ።

«ይሕ የማረጋጋቱ ሥራ አንድ ገፅታ ነዉ።ዋና አላማዎቹም የሠላማዊዉን ሕዝብ ደሕንነት መጠበቅ፥ የሰሜናዊ ማሊን አስተዳደር ዳግም ማደራጀት፥ አስቸኳይ ሠብአዊ ድጋፎችን ማድረግ፥ ምርጫን ማደራጀት፥ ሥደተኞችን ወደቀያቸዉ እንዲመለሱ ማድረግ እና ሰማናዊ ማሊ ዉስጥ የዕለት ከዕለት ሠላማዊ ኑሮን ማስፈን ናቸዉ።»

ተልዕኮዉ ሠላም ማስከበር፥ ዉጊያ ይሁን እርዳታ ማቀበል MINUSMA በሚል ምሕፃረ-ቃል ይጠራል።አስራ-ሁለት ሺሕ ስድስት መቶ ወታደሮች እና አንድ ሺሕ አራት መቶ ፖሊሶችን ያስተናብራል።እስካሁን አፍሪቃ መራሽ ዓለም አቀፍ የማሊ ደጋፊ ተልዕኮ (AFISMA በምሕፃሩ) የሚባለዉን የአፍሪቃ ሕብረት ተልዕኮን ከመጪዉ ሐምሌ ጀምሮ ይተካል።

የማሊ ጦር ሐይል መኮንኖች የሐገሪቱን መሪ አስወግደዉ ሥልጣን በመያዛቸዉ ምክንያት የተፈጠረዉን ፖለቲካዊ ቀዉስ ለማስወገድ ቀዳሚዉ የአፍሪቃ ሕብረት ነበር።የማሊ አክራሪና የቱዓሬግ አማፂያን ወደ ርዕሠ-ከተማ ባማኮ መገስገሳቸዉን ለማስቆም ቀድመዉ የተንቀሳቀሱት ጦር ያዘመቱትም አፍሪቃዉያን ናቸዉ።

አፍሪቃዉያን የራሳቸዉን ችግር እራሳቸዉ መፍታት አለባቸዉ በማለት ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ የነበሩት ምዕራባዉያን ሐገራት የወትሮ አቋማቸዉን ሽረዉ የቀድሞዋ ቅኝ ገዢ ፈረንሳይ ዘላ ገባች።ተሻራኪዎችዋም ሙሉ ድጋፍ ሰጧት።የአፍሪቃ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳት ወይዘሮ ድላሚኒ ዙማ ባለፈዉ አርብ እንዳሉት የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት ፈረንሳይ ያረቀቀችዉን የዉሳኔ ሐሳብ ሲያፀድቅም የአፍሪቃዉያን የእስካሁንና የወደፊት አስተዋፅኦ ከቁብ አልቆጠረዉም።

«ዉሳኔዉን እንቀበለዋለን ልበል።ግን በሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተሳትፈን ቢሆን ኖሮ እኛ በተለየ መንገድ የምንመለከታቸዉ ጉዳዮች ይኖሩ ነበር።ምክንያቱም የዉሳኔዉ አብዛኛ ክፍል የአፍሪቃ ሕብረትን ሐሳቦችና እርምጃዎችን አድበስብሶ ሁሉንም ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ይሰጣል።በመሠረቱ ግን የማሊ ሁኔታ የጋራ ተልዕኮ ነዉ።እንዲያዉም በአንዳድ መስኮች የተወሰዱትን እርምጃዎች የመራዉ የአፍሪቃ ሕብረት ነዉ።»

የሞሮኮ ማዕከላዊ መንግሥት እና ፖሊሳሪዮ የተሰኘዉ የምዕራብ ሳሕራዊ ግዛት ነፃአዉጪ ድርጅት በ1991 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ) ባደረጉት የሠላም ሥምምነት መሠረት የአወዛጋቢዋ ግዛት ፖለቲካዊ አስተዳደር በግዛቲቱ ሕዝብ ድምፅ መወሰን ነበረበት።ሁለቱን ወገኖች የሸመገለዉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥምምነቱን ገቢራዊነትና ሕዝበ-ዉሳኔዉን የሚከታተሉ ከሁለት መቶ ሐምሳ በላይ ዓለም አቀፍ ወታደሮችን አስፍሯል።ሠራዊቱ አሁንም እዚያዉ ነዉ። ሕዝበ-ዉሳኔዉ ግን አልተደረገም።ሃያ-ሁለት ዓመቱ።

የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አረጋጊ ተልዕኮ (MONUC) የተሰየኘዉ ከአስራ-ስምንት ሺሕ በላይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሠላም አስከባሪ ሠራዊት ኮንጎ ከሠፈረ ዘንድሮ አስራ-ሰወስት ዓመቱ።ኮንጎ ዛሬም ሠላም የለም።ዳርፉር ሠላም አስከባሪ ሠራዊት ሠፍሯል።ሠላም አለ ማለት ግን ያስዋሻል። የአፍሪቃ ሕብረት ሶማሊያ ያሠፈረዉ ሠራዊት ተልዕኮ በርግጥ አሸባብን መዉጋት እንጂ ሠላም ማስከበር ነዉ ማለት ሐሰት ነዉ።አሸባብ ግን ዛሬም ሞቃዲሾን ያሸብራል።

የቀድሞዎቹ የኮትዲቯር አማፂያንና የሐገሪቱ መንግሥት ያደረጉትን የሠላም ዉል ለማስከበር የዘመተዉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሠላም አስከባሪ ሠራዊት ከፈረንሳይ ጦር ጋር ተባባሮ የቀድሞዉን የሐገሪቱን ፕሬዝዳት ሎራ ባግቦን ታማኞችን በመዉጋትና ፕሬዝዳንቱን በመማረክ እዉነተኛ ተልዕኮዉን አስመስክሯል።

ተልዕኮዉ በትክክል ሠላም ማስከበር፥ የማይፈለግ ሐይልን መዉጋት፥ ወይም የላኪዎችን ጥቅም ማስከበር ማሊን ጨምሮ ባሁኑ ወቅት በዘጠኝ በአፍሪቃ ሐገራት የዉጪ ሠራዊት ሠፍሯል።በየዓመቱ በትንሽ ግምት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ይወጣል።ታዲያ አፍሪቃ ነፃ እና ሠላምስ ናት? ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰማን።

ነጋሽ መሐመድ

HANDOUR - Soldaten aus Togo treffen in am 17.01.2013 in Mali ein. Die Soldaten beteiligen sich an der Operation «Serval» in Mali. Foto: Jeremy Lempin EMA / ECPA-D dpa (ACHTUNG REDAKTIONEN: Nur zur redaktionellen Verwendung im Zusammenhang und Nennung des Urhebers.) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ማሊ-የቶጎ ጦርምስል picture alliance / dpa
French soldiers pass a donkey-driven cart outside the destroyed main market in Gao, March 2, 2013. French soldiers visited the market on Saturday, nine days after it was destroyed during fighting between radical Islamists and Malian and French soldiers. REUTERS/Joe Penney (MALI - Tags: CIVIL UNREST CONFLICT MILITARY POLITICS)
ማሊ-የፈረንሳይ ጦርምስል Reuters
British Foreign Minister William Hague speaks at an Australian-British Chamber of Commerce lunch in Sydney, Wednesday, Jan. 19, 2011. Hague is visiting Australia for the Australia-United Kingdom Ministerial Consultations. (AP Photo/Rick Rycroft)+++Bitte nicht für FLASH Galeiren verwenden.+++
ሔግምስል AP

ሒሩት መለሠ