1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ኅብረት፣ መፈንቅለ መንግሥትና ፈታኙ አቋም

እሑድ፣ ሐምሌ 7 2005

አንድ ቢሊዮን ገደማ ህዝብ ባለው ክፍለ ዓለም 54 አባል ሃገራትን ያቀፈውና ዘንድሮ 50 ኛ ዓመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የአፍሪቃ ኅብረት በየጊዜው በሚከሠቱ የአህጉሩ ችግሮች መፈተኑ አልቀረም ። የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ወይዘሮ እንኮሳዛና ድላማኒ

https://p.dw.com/p/1977R
ምስል Getachew Tedla HG

ዙማ ፣ በቅርቡ በግብጹ ፕሬዝዳንት መሐመድ ሙርሲ ከሥልጣን ገለል እንዲሉ የተደረገበትን እርምጃ መነሻ በማድረግ ፤ኅብረቱ ከግብፅ ህዝብ ጎን እንደሚቆም ፤ሆኖም አገሪቱ ለጊዜው ከአባልነት እንደምትታገድ መጠቆማቸው የሚታወስ ነው ። ይህ ጊዜያዊ ወይስ ዘለቄታ ያለው የኅብረቱ መርኅ ነው? «የአፍሪቃ ኅብረት፣ መፈንቅለ መንግሥትና ፈታኙ አቋም ፣»የዛሬው የእንወያይ ዝግጅት ትኩረት ነው በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር 3 እንግዶችን ጋብዘናል ። እነርሱም

1.የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር፣እንዲሁም የኦሮሞ ፌደራል ኮንግረስ ሊቀመንበር ፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና

2.የፀጥታ ጥናት ተቋም ባልደረባ ዶክተር ሰሎሞን አየለ ደርሶ እንዲሁም

3. የቀድሞ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ባልደረባና ጋዜጠኛ አቶ ንጉሤ ደስታ ናቸው

ተክሌ የኋላ

ልደት አበበ