1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ኅብረት ጉባኤና ትኩረቱ

ረቡዕ፣ ጥር 18 2003

የአፍሪቃ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ በደስታና በችግር መካከል እንደሚካሄድ የህብረቱ ምክትል ዋና ጸሐፊ ኤራስቶስ ሙዋንቻ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አመለከቱ።

https://p.dw.com/p/QvhC
የአፍሪቃ ኅብረትምስል DW /Maya Dreyer

ደስታዉ ኅብረቱ በተለይ በሰላምና ደህንነት ምክር ቤቱ በኩል ያከናወናቸዉ ሥራዎች ዉጤት እያሳዩ በመሆኑ ሲሆን ችግሩ ደግሞ በአፍሪቃ የተለያዩ ክፍሎች ድንገተኛ ዉጥረቶች እየሰፈኑ ባሉበት ወቅት መካሄዱ እንደሆነ ምክትል ዋና ጸሐፊዉ አስረድተዋል። ይህም የመሪዎችን ከፍተኛ ቁርጠኝነት የሚጠይቁ ዉሳኔዎችን ማሳለፍ እንደሚጠይቅ ተገልጿል። ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸዉ ወቅታዊ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።

ታደሰ እንግዳዉ ፣

ሂሩት መለሰ

ሽዋዬ ለገሰ