1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ አብያተ ክርስቲያንና ግብረሰዶማዊነት

ዓርብ፣ ኅዳር 21 2005

ናይጀሪያ ውስጥ ግብረ ሰዶማዊ ግንኙነት ያላቸው ወይም ለግብረሰዶማውያን መብቶች ዘመቻ የሚያካሂዱ እስከ 10 አመት የሚደርስ እሥራት ሊጠብቃቸው ይችላል ። ይህ ህግ ሥራ ላይ እንዲውል የናይጀሪያው ፕሬዝዳንት ጉድ ላክ ጆናታን ማፅደቅ አለባቸው ።

https://p.dw.com/p/16tHP
Homosexuelle in Nigeria Eingereicht von: Christine Harjes - Bildautor: Katrin Gänsler
ምስል Katrin Gänsler
Members of the Uganda National Pastors Task Force Against Homosexuality demonstrate in front of the Royal Danish embassy in Kampala, Uganda Tuesday, Dec. 22. 2009. The group went on Kampala streets, near embassies and high commission offices telling the international community to back off from their criticism of the anti homosexual bill that is in the making in Parliament. The law that threatens a death sentence to homosexuals has attracted critics including US President Barack Obama among others. Sweden has threatened to cut aid to Uganda. (AP Photo/Stephen Wandera)
ምስል AP

በብዙዎቹ የአፍሪቃ ሃገሮች የግብረ ሰዶማውያን መብት እንዲጠበቅ የሚቀርበው ጥሪ በአብያተ ክርስቲያን ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም ። የአብያተ ክርስቲያን ተጠሪዎችና ህብረተሰቡ ግብረሰዶማዊነት ከባህላችንና ልምዳችን ውጭ በመሆኑ መቼም ቢሆን አንደግፈውም ይላሉ ። ይህ ጠንካራ አቋምም በፖለቲካ ውሳኔዎች ላይ ተፅእኖ እያደረገ ነው ። በዚህ ረገድ ማላዊ እንደ አንድ ምሳሌ ልትወሰድ ትችላለች ።
« የግብረ ሰዶማውያንን መብት በመቃወም ስብሰባ አድርገናል ። የናይጀሪያ ካቶሊካውያን ማህበረሰብ እንዲሁም የተለያዩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ግብረሰዶማዊነት የሚቃወሙ መፈክሮችን አሳይተዋል ። »
ቄስ ራፋኤል አደባዮ የሌጎስ ናይጀሪያው የቅዱስ አግነስ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ካህን ናቸው ። በናይጀሪያ የክርስትና እምነት ተከታዮች ግብረ ሰዶማዊነት በፅኑ ይቃወማሉ ። ቄስ አደባዮ ምክንያቱን ያስረዳሉ ።
« እግዜዘብሔር የሚቃወመውን ቤተክርስቲያን መደገፍ አትችልም ። ፀያፍ ነው »
በናይጀሪያ ክርስትና እስልምናም ሆነ ልምዳዊ እምነቶች የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን እንደሚቃወሙ የናይጀሪያ የፓርላማ አባል የሆኑት ጃጋባ አደምስ ጃጋባ ይናገራሉ ።
« ልምዳዊ እምነቶቻችን ይቃወሙታል ፤ ክርስትና አይቀበለውም ፤ እስልምናም ይቃወመዋል ። በባህላችን ፀያፍ ነው ። ለዚህም ነው እንደ ፓርላማ ባህላችንንና ልምዶቻችንን ለማስጠበቅ ህጉን ያሳለፍነው ። »
ናይጀሪያ ባህልና ልምድዋን ለማስጠበቅ ህግ አውጥታለች ። ናይጀሪያ ውስጥ ግብረ ሰዶማዊ ተጓዳኝነት ወይም ለግብረሰዶማውያን መብቶች ዘመቻ የሚያካሂዱ እስከ 10 አመት የሚደርስ እሥራት ሊጠብቃቸው ይችላል ። ይህ ህግ ሥራ ላይ እንዲውል የናይጀሪያው ፕሬዝዳንት ጉድ ላክ ጆናታን ማፅደቅ አለባቸው ። አብያተ ክርስቲያን ግብረ ሰዶማዊነት መቃወማቸው በ ጀርመን Recklinghausen ለግብረ ሰዶማውያንንና አብያተ ክርስቲያን የጋራ የምክክር ቡድን መሪ Markus Gutfleisch አያስገርምም ።

« የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሁሌም ጣልቃ ትገባለች ፤ ለምሳሌ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ መንግሥት ለግበረሰዶማውያን የበለጠ መብት የሚሰጥ አንድ ረቂቅ ህግ ሲያቀርብ ይቃወማሉ ። »
ጉትፍላይሽ አብያተ ክርስቲያን በማህበራዊ ጉዳዮች የራሷን ሃሳብ ማንፀባረቋ በመሰረቱ ተገቢ ነው ። ሆኖም በርሳቸው አመለካከት በወግ አጥባቂ አመለካከት ሳቢያ ግን የሰው ልጅ መብት መጣስ የለበትም ። ይህ የማሊን መንግሥት አስቸጋሪ ምርጫ ውስጥ ከቶታል ።
አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን የሃገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የግብረሰዶማውያንን እንቅስቃሴ የሚያግደው ህግ እንደሚነሳ መናገራቸውን ዘግበዋል ። ይህ ጉዳይም በሃገሪቱ ፓርላማ ክርክር እየተካሄደበት ነው ። አስተያየቱ ከማላዊ አብያተ ክርስቲያን ምክር ቤት በኩል አሉታዊ ምላሽ አስከትሏል ። ማላዊ ያሉ አንዳንድ ግብረ ሰዶማውያን ምክር ቤቱ እንደ ሰው እንደማያቆጥራቸውና በነፃነት መንቀሳቀስ ሊፈቀድላቸው አይገባም እንደሚልም ይናገራሉ ። አብያተ ክርስቲያን ስለ ሰብአዊ መብት መናገር እየወደዱ የነርሱን መብት አለመጠበቃቸው ከምድረ ገፅ ይጥፉም ማለታቸውን እአይቀበሉም ። ቄስ አዴባዮ ግን ይሄ ከእምነታችን ጋር የሚሄድ አይደለም ነው የሚሉት ።
«ቤተክርስቲያን ሰብአዊ መብትን ልታከብር ትችላለች ። ሰብአዊ መብት የእግዜአብሔርን ትዕዛዛት ሲጥስ ግን እስከ ወዲያኛው አንደግፈውም »

በማላዊ አብያተ ክርስቲያን ተቃውሞ በኋላ መንግሥት በመጀመሪያው አቋሙ ከመፅናት ወደ ኋላ እያለ ነው ። የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለው ከአፍሪቃ የግብረ ሰዶማውያን መብት በህገ መንግሥት ያሰፈረችውና እና የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ የፈቀደችው ደቡብ አፍሪቃ ብቻ ናት ። በተቀሩት ሃገራት በሙሉ ማለት ይቻላል ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት በእሥራት ያስቀጣል ። በካሜሩን ከ 6 ወር እስከ 5 አመት በሚደርስ እሥራት እንዲሁም 350 ዩሮ ያስቀጣል ። ናይጀሪያ ና ኡጋንዳ የግብረ ሰዶማዊነት የሚቃወም ህግ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ናቸው ። ግብረሰዶማዊነትን የሚቃወም ህግ ከሌላቸው ጥቂት የአፍሪቃ ሃገራት ውስጥ ማሊ ቡርኪናፋሶና አይቮሪ ኮስት ይገኙበታል ።
ሂሩት መለሰ

A Ugandan man reads the headline of the Ugandan newspaper "Rolling Stone" in Kampala, Uganda. Tuesday, Oct. 19, 2010, in which the papers reveals the identity of allegedly gay members of Ugandan society and calls for public punishment against those individuals. The "Rolling Stone" is a fairly new publication under the management of Giles Muhame, a Ugandan journalist..rights activitists say that at least four homosexuals have been attacked since a Ugandan newspaper published an article this month called "100 Pictures of Uganda's Top Homos Leak _ Hang Them." A year after a Ugandan legislator tried to introduce a bill that would have called for the death penalty for being gay, rights activists say homosexuals face a host of hostility. (AP Photo)
ምስል AP

አርያም ተክሌ