1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያውያን አይሁዶች አቀባበል

ሐሙስ፣ ነሐሴ 23 2005

ቀሬ ቤተእስራኤላውያን ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ የትናንቱ ጉዞ የመጨረሻው እንዳይደለ ቤተ እስራኤላዊ የፓርላማ አባል ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ። ትንናት እስራኤል የገቡት ኢትዮጵያውያን አይሁዶች እጎአ በ2010 መጨረሻ ላይ ኢትዮጵያ የሚገኙ ቀሪ የቤተ እስራኤል ወገኖች በ 3 ዓመት ውስጥ ተጠቃለው እስራኤል እንዲገቡ በታቀደው መሠረት የተከናወነ ነው።

https://p.dw.com/p/19Yjl
ምስል imago

ላለፉት 30 ዓመታት እስራኤል ከኢትዮጵያ ቤተ እስራኤላዉያንን ስትወስድበት የነበረዉን ዘመቻ ማጠናቀቋን ከቴልአቪቭ የወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ። አዣንስ ፍራንስ ፕረስ እንደዘገበዉ ዘመቻ «የእርግብ ክንፎች» በተሰኘዉ ጉዞ የመጨረሻዎቹ 450 ቤተ እስራኤላዉያን በሁለት አዉሮፕላን ትናንት ቴል አቪቭ አዉሮፕላን ማረፊ ደርሰዋል። እንደዘገባዉ የአይሁድ ዝርያ አለን የሚሉ ሌሎች ኢትዮጵያዉያን ከእንግዲህ ወደእስራኤል የሚገቡት በተናጠል ይሆናል። እስራኤል ይህ ዘመቻ ከተጀመረ ከጎርጎሪዮሳዊዉ 1984ዓ,ም አንስቶ አንድ መቶ ሺህ ገደማ ቤተ እስራኤላዉያንን ከኢትዮጵያ መዉሰዷ ገልጿል።

Jerusalem - Felsendom
ምስል picture-alliance/dpa

ትናንት በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት ደጃፍ ለሰልፍ የወጡ አምስት መቶ የሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን አይሁዶች ገና 5000 ወገኖቻቸዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ እንደቀሩ አመልክተዋል። ተሰላፊዎቹ የአይሁድ እምነትን ይከተላሉ የሚል እዉቅና ያልተሰጣቸዉ ቀሪ ወገኖቻቸዉን ወደእስራኤል የማምጣቱ ሂደት እንዳይቋረጥም ተማጽነዋል።

ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል በመግባት የመጨረሻዎቹ የተባሉት 450 የሚደርሱ ቤተ እስራኤላውያን ትናንት ቴላቪቪ እስራኤል ሲደርሱ ይፋ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ። በአቀባበሉ ላይ የእስራኤል ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ቤተ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል ። በሌላ በኩል ቀሬ ቤተእስራኤላውያን ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ የትናንቱ ጉዞ የመጨረሻው እንዳይደለ ቤተ እስራኤላዊ የፓርላማ አባል ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ። ትንናት እስራኤል የገቡት ኢትዮጵያውያን አይሁዶች እጎአ በ2010 መጨረሻ ላይ ኢትዮጵያ የሚገኙ ቀሪ የቤተ እስራኤል ወገኖች በ 3 ዓመት ውስጥ ተጠቃለው እስራኤል እንዲገቡ በታቀደው መሠረት የተከናወነ መሆኑን የእስራኤል ወኪላችን ግርማው አሻግሬ ዘግቧል ።

ግርማው አሻግሬ

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ