1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ መንግሥት መግለጫ

ዓርብ፣ የካቲት 18 2008

አቶ ጌታቸው ረዳ ትናንት ለውጭ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በተለይ በምዕራብ አርሲ የሰዎች ህይወትና ንብረት የጠፋበት መሣሪያ የታጠቁ ኃይሎች ያባባሱት ግጭት ከህዝብ ጥያቄ ጋር የሚገናኝ እንዳልሆነ ተናግረዋል ።

https://p.dw.com/p/1I2z3
Äthiopien Minister Getachew Reda
ምስል DW/G. Tedla

[No title]

በኦሮምያ ክልል ከተከሰቱት ግጭቶች አንዳንዱ ከውጭ ድጋፍ ባላቸው መሣሪያ በታጠቁ ቡድኖች የሚካሄድ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ ። የኢትዮጵያ መንግሥት የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ትናንት ለውጭ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በተለይ በምዕራብ አርሲ የሰዎች ህይወትና ንብረት የጠፋበት መሣሪያ የታጠቁ ኃይሎች ያባባሱት ግጭት ከህዝብ ጥያቄ ጋር የሚገናኝ እንዳልሆነ ተናግረዋል ። መንግሥት በየአካባቢው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስም ህብረተሰቡን እያወያየ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልፀዋል ። ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል ።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ