1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ምርጫና የሸንጎ መግለጫ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 3 2006

በሸንጎዉ መግለጫ መሠረት ነፃ ምርጫ ለማድረግ እስመራጭ ኮሚሽን፤መገናኛ ዘዴዎች፤ፍርድ ቤቶች፤ ሕግና ፀጥታ አስከባሪዎች ገለልተኛ መሆን አለባቸዉ

https://p.dw.com/p/1BgWx

በመጪዉ ዓመት (2007) ኢትዮጵያ ዉስጥ ሊደረግ የታቀደዉ ምርጫ ነፃና ፍትሕዊ እንዲሆን የሚመለከታቸዉ አካላት አስፈላጊዉን ዝግጅት ካሁኑ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ጠየቀ።ርዕሠ-መንበሩን ሰሜን አሜሪካ ያደረገዉ ሸንጎ አንደሚለዉ ምርጫዉን ነፃ፤ ፍትሐዊና ሁሉን አሳታፊ ለማድረግ ገዢዉ ፓርቲ ኢሕአዴግ፤ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ሕዝቡ የየበኩላቸዉን ሐላፊነት መወጣት አለባቸዉ።በሸንጎዉ መግለጫ መሠረት ነፃ ምርጫ ለማድረግ እስመራጭ ኮሚሽን፤መገናኛ ዘዴዎች፤ፍርድ ቤቶች፤ ሕግና ፀጥታ አስከባሪዎች ገለልተኛ መሆን አለባቸዉ።የዋሽግተን ዲሲ ወኪላችን አበበ ፈለቀ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

አበበ ፈለቀ

ነጋሽ መሐመድ

ሒሩት መለሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ